Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

ዓለምአቀፋዊ ዜና

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቻይና የስራ ጉብኝት እያደረጉ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቻይና ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ፕሬዚዳንቱ ትናንት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ቤጂንግ የገቡ ሲሆን÷በቆይታቸውም ከቻይናው ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ችያንግ ጋር በሀገራቱ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡…

በቱርክ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊውን ለመለየት 2ኛ ዙር ድምጽ እንደሚሠጥ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቱርክ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ተፎካካሪዎች አብላጫ ድምጽ ባለማግኘታቸው ወደ 2ኛ ዙር ድምጽ የመስጠት ሂደት ተሸጋግሯል። እስካሁን ባለው ሂደት የወቅቱ የሀገሪቷ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ታይፕ ኤርዶኻን 49 ነጥብ 37 በመቶ ድምፅ አግኝተዋል፡፡ የእርሳቸው…

በቱርክ ፕሬዚዳንታዊና የፓርላማ ምርጫ ድምፅ መስጠት ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቱርክ ፕሬዚዳንታዊ እና የፓርላማ ምርጫ ድምፅ መስጠት ተጀምሯል፡፡ ለሚቀጥሉት አምሥት ዓመታት ሕዝብ ያገለግሉኛል ያላቸውን ፕሬዚዳንት እና የፓርላማ አባላት ለመምረጥ ከ64 ነጥብ 1ሚሊየን በላይ ሰዎች ተመዝግበዋል። በዚህም በሚሊየኖች የሚቆጠሩ…

ሶማሊያ በምዕራባውያን ተደግፋ ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት ማረጋገጥ አትችልም – የሀገሪቱ መሪ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ሶማሊያ በምዕራባውያን ተደግፋ ዘላቂነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት ማረጋገጥ አትችልም ሲሉ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኸ ሞሀሙድ ተናገሩ፡፡ ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት ፥ መንግስታቸው በሀገሪቱ ባለጠጋዎች እና ኩባንያዎች ላይ ከፍ ያለ ቀረጥ ለመጣል…

ጀርመን ለዩክሬን ከፍተኛ የተባለውን የጦር መሳሪያ ድጋፍ ይፋ አደረገች

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 5 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጀርመን ÷ ለዩክሬን 2 ነጥብ 7 ቢሊየን ዩሮ የሚያወጣ የጦር መሳሪያ ድጋፍ ይፋ አድርጋለች፡፡ ድጋፉ የሆነው የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ በተያዘው ሳምንት በበርሊን የስራ ጉብኝት ለማድረግ ማቀዳቸውን ተከትሎ ነው ተብሏል ፡፡…

የቀድሞው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር የሁለት ሣምንታት የዋስትና ጊዜ ተፈቀደላቸው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፓኪስታን ፍርድ ቤት በዚህ ሣምንት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ለእስር ለተዳረጉት የቀድሞው የሀገሪቷ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካን የሁለት ሣምንታት የዋስትና ጊዜ ፈቀደ። የኢስላማባድ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አርብ ዕለት በዋለው ችሎት ነው በሙስና ሰበብ…

ዶናልድ ትራምፕ ለተላለፈባቸው የ5 ሚሊየን ዶላር የፆታዊ ትንኮሳ ካሳ ይግባኝ ጠየቁ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፈፅመዋል ለተባለው ፆታዊ ትንኮሳ ለተበየነባቸው የ5 ሚሊየን ዶላር ካሳ ይግባኝ ጠየቁ፡፡ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ላይ የተላለፈው ብይን ከሁለት ቀናት በፊት ባሳለፍነው ማክሰኞ ከሰዓት በኋላ ነው በኒውዮርክ…

ሩሲያ በነዳጅ ግብይት ከአውሮፓ ኅብረት ጋር እየተለያየች ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የምዕራባውያንን ማዕቀብ ተከትሎ ሩሲያ ወደ ላቲን አሜሪካ የምትልከውን የነዳጅ አቅርቦት መጠን ማሳደጓ ተገለጸ፡፡ አሁን ላይ የወጣው የቁጥር መረጃ እንደሚያመለክተው በፈረንጆቹ ሚያዝያ ወር ላይ ሩሲያ ፕሪሞርስክ ከተሰኘው የባልቲክ ወደቧ ሁለት 73…

ፕሬዚዳንት ኤርዶኻን ለመንግስት ሰራተኞች 45 በመቶ የደመወዝ ጭማሪ አደረጉ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 2 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይፕ ኤርዶኻን ለመንግስት ሰራተኞች 45 በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ማድረጋቸውን አስታወቁ፡፡   ፕሬዚዳንት ኤርዶኻን የደመወዝ ጭማሪውን ያደረጉት በፈረንጆቹ የፊታችን ግንቦት 14 ቀን የሚካሄደውን አጠቃላይ…

ፔንታገን ለዩክሬን የ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር እርዳታ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ መከላከያ መስሪያ ቤት ለዩክሬን ወታደራዊ እርዳታ የሚውል 1 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ የገንዘብ እርዳታው በዋናነት የዩክሬንን መከላከያ የማጠናከር አላማ ሲኖረው፥ በተለይም ለአየር መቃወሚያ፣ ለጦር መሳሪዎች እና…