Fana: At a Speed of Life!

የትግራይ ሕዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሰላሙን እንዲጠብቅ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ከፍጻሜ እንዲደርሱ ሕዝቡ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሰላሙን እንዲጠብቅ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መሥተዳድር ጌታቸው ረዳ ጥሪ አቀረቡ፡፡ ርዕሰ መሥተዳድሩ በትግራይ ደቡብ ምሥራቅ ዞን በሕዝብ ከተወከሉ የተለያዩ…

በሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1 እስከ 4 በመውጣት አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በበርሊን 2024 የሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1 እስከ 4 በመውጣት አሸንፈዋል፡፡ በዚሁ መሠረት አትሌት ትዕግስት ከተማ ርቀቱን 2 ሠዓት ከ16 ደቂቃ ከ42 ሰከንድ በመግባት አሸንፋለች፡፡ እንዲሁም አትሌት መስታወት…

አቶ ኦርዲን በድሪ በክልሉ የለማውን የማሽላ ኢንሼቲቭ ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች በክልሉ በኩታ ገጠም የለማውን የማሽላ ኢንሼቲቭ ጎበኙ፡፡ "መልካም" የተባለውና ከፍተኛ ምርት የሚሰጠውን ማሽላ በክልሉ የማስፋፋት ስራ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል።…

በበርሊን ማራቶን አትሌት ሚልኬሳ መንገሻ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በበርሊን 2024 ማራቶን አትሌት ሚልኬሳ መንገሻ አሸነፈ፡፡ አትሌት ሚልኬሳ ርቀቱን 2 ሠዓት ከ3 ደቂቃ ከ17 ሰከንድ በማጠናቀቅ ውድድሩን ማሸነፍ ችሏል፡፡ እንዲሁም አትሌት ሐይማኖት አለው 2 ሠዓት ከ3 ደቂቃ ከ31 ሰከንድ በመግባት 3ኛ…

ከንቲባ አዳነች አቤቤ 75 የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ ክፍለ ከተማ ባለ 5 ወለል 75 የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላለፉ፡፡ በዊንጌትና ገብስ-ተራ የቀበሌ ቤቶችን በማፍረስ ለመኖር ምቹ የሆኑ 75 የመኖሪያ ቤቶች ያላቸው ባለ 5 ወለል…

ኢትዮጵያ በሶማሊያ የደረሰውን የሽብር ጥቃት አወገዘች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግሥት በሶማሊያ ሞቃዲሾ የደረሰውን የሽብር ጥቃት አወገዘ፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ባወጣው የሐዘን መግለጫ÷ በተፈጸመው የሽብር ጥቃት ሕይወታቸውን ላጡ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡ የተፈጸመውን ጥቃት በማውገዘ ሽብርተኝነትን…

በቡና ምርታማነትና ጥራት ላይ ያተኮረ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡና ምርታማነትና ጥራት ላይ ትኩረት ያደረገ የንቅናቄ መድረክ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ በመድረኩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡…

አቶ አረጋ ከበደ የሕዝብን ጥያቄ ለመመለስ የፍትሕ ተቋማት ሠራተኞች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳሰቡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብን ጥያቄ ለመመለስ የፍትሕ ተቋማት ሠራተኞች የሕዝብ አገልጋይነት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አሳሰቡ፡፡ በባሕር ዳር እየተካሄደ በሚገኘው የአማራ ክልል የዳኝነትና ፍትሕ አካላት የትብብር…

የዩኔስኮ ዓለም አቀፍ ምርምር ፎረም ከነገ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) ዓለም አቀፍ የምርምር ፎረም በአዲስ አበባ ከነገ ጀምሮ እንደሚካሄድ የአፍሪካ ሕብረት አስታወቀ። ፎረሙን የአፍሪካ ሕብረት እና ዩኔስኮ በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን÷…

ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በፍትሕ ሥርዓት ግንባታ ሂደት በጋራ ለመሥራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በፍትሕ ሥርዓት ግንባታ ሂደት፣ በሕግ ትብብር ጉዳዮች እና በጋራ ጥቅም ላይ አብረው ለመሥራት ተስማሙ፡፡ በፍትሕ ሚኒስትር ዴዔታ ተስፋዬ ዳባ የተመራ ልዑክ በአዘርባጃን እየተካሄደ በሚገኘው 29ኛው ዓለም አቀፍ የዐቃቤ…