Fana: At a Speed of Life!

የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ልዑክ በገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው አደጋ የተጎዱ ወገኖችን አጽናና

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ልዑክ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ የመሬት መንሸራተት አደጋ በተከሰተበት ቦታ በመገኘት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 85 ቶን የሰብዓዊ ድጋፍ አስረክቧል። በተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ፕሬዚዳንት ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ የተላከው…

በተከዜ ወንዝ በጀልባ ተሳፍረው ሲጓዙ የነበሩ 12 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዋግ ኸምራ ብሔረ-ሰብ አስተዳደር ከሰሃላ ሰዬምት ወረዳ ወደ ዝቋላ ወረዳ በተከዜ ወንዝ በጀልባ ሲጎዙ የነበሩ 12 ሰዎች በድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ሕይወታቸው አልፏል፡፡ መነሻቸውን ሰሃላ ሰዬምት ወረዳ መሸሃ ከተማ እና ሰላዝጌ ቀበሌ አድርገው ወደ…

በይርጋጨፌ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሶስት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ አደጋው መነሻውን ሞያሌ ያደረገና የአፈር ማዳበሪያ የጫነ ከባድ ተሽከርካሪ ከሞተር ሳይክል ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡ የትራፊክ አደጋው በይርጋጨፌ ወረዳ…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአጀንዳ ልየታ የምክክር መድረክ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በክልሉ የባለድርሻ አካላት የአጀንዳ ልየታ መድረክና ለሀገራዊ ምክክሩ ጉባኤ ተወካዮች ምርጫ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት እንደሚከናወን ተገለፀ፡፡ በሂደቱ በክልሉ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ወኪሎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግስት አስፈጻሚ…

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለ2017 በጀት ዓመት ከ8 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ለክልሉ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ማስፈጸሚያ የሚሆን ከ8 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጽድቋል፡፡ የክልሉ ምክር ቤት ባካሄደው ጉባዔ ለ2017 በጀት ዓመት 8 ቢሊየን 974 ሚሊየን 531 ሺህ 586 ብር…

ከ40 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከ40 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት ጋር ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱ በቀጣዩ ዓመት የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት በመላ ሀገሪቱ በሚያካሄደው የግብርና…

አምራቾች በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ላይ በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በመጠጥ ዘርፍ የተሰማሩ አልሚዎች በሥራ ሒደት በሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች ላይ በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ ተገልጿል። በኢትዮጵያ በመጠጥ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ አምራቾች ፎረም ተካሂዷል። ፎረሙ በዘርፍ የተሰማሩ አልሚዎች ከገበያ ፉክክር ባለፈ…

እስራኤል በጎላን ተራራ ሂዝቦላ ያደረሰባትን ጥቃት ተከትሎ ሊባኖስን በቦንብ ደበደበች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) እስራኤል በጎላን ተራራ ሂዝቦላ አድርሶብኛል ያለችውን ጥቃት ተከትሎ ሊባኖስን በቦንብ መደብደቧ ተነግሯል፡፡ የእስራኤል ጦር በማእከላዊ ዴር ኤል ባላ ውስጥ ለመስክ ሆስፒታል እና ለመጠለያነት በሚያገለግል ትምህርት ቤት ላይ ጥቃት በመሰንዘር 15…

የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ተካሂዷል። "የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ባለው የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች…

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀረሪ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ በሚገኝው 6ኛ ዙር 3ኛ አመት 6ኛ መደበኛ ጉባኤ የቀረበለትን የካቢኔ አባላት ሹመት ተቀብሎ አጽድቋል። የካቢኔ አባላት ሹመት በምክር ቤቱ የጸደቀው በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ አቅራቢነት ነው።…