Fana: At a Speed of Life!

በኢንዱስትሪ ፓርኮች የቻይና ባለሀብቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢንዱስትሪ ፓርኮች የቻይና ባለሀብቶችን ተሳትፎ ይበልጥ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ ተናገሩ፡፡ ዋና ስራ አስፈፃሚው ከቻይና ሁናን ግዛት ለመጡ የተለያዩ ኩባንያዎች ተወካዮች ጋር…

በሚያዝያ ወር ብቻ ከ51 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሚያዝያ ወር 2016 ዓ.ም ብቻ ከ51 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በሚያዝያ ወር 51 ነጥብ 51 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 51 ነጥብ 07 ቢሊየን ብር ወይም የእቅዱን 99 ነጥብ 16 በመቶ መሰብሰብ…

ኮማንድ ፖስቱ እየወሰደ ባለው ሕግ የማስከበር ዘመቻ ቀጣናውን የተረጋጋ ማድረግ ተችሏል – ሌ/ጄ ብርሃኑ በቀለ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የባህርዳር-ጎንደር ኮማንድ ፖስት በጽንፈኛው ቡድን ላይ እየወሰደ ባለው ሕግ የማስከበር ዘመቻ ቀጣናውን ሠላማዊና የተረጋጋ ማድረግ ተችሏል ሲሉ የኮማንድ ፖስቱ ሰብሳቢና የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌ/ጄ ብርሃኑ በቀለ ገለጹ፡፡ ኮማንድ ፖስቱ…

ዘመኑን የሚመጥን የገቢ አሰባሰብ ስርአት መከተል ይገባል – ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያን የገቢ መጠን ለማሳደግ ከተለምዷዊ አሰራር የተላቀቀና ዘመኑን የሚመጥን የገቢ አሰባሰብ ስርዓት መከተል ይገባል ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳሰቡ። የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የ2016…

90 በመቶ የሚሆነው የሩሲያና ቻይና ግብይት በሀገራቱ መገበያያ ገንዘብ መፈጸሙ ተነገረ 

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 90 በመቶ የሚሆነው የሩሲያና ቻይና ግብይት በሀገራቱ መገበያያ ገንዘብ የተፈጸመ መሆኑን የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ገለፁ፡፡ ፕሬዚዳንት ፑቲን ለሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ትናንት ቤጂንግ የገቡ ሲሆን ከቻይናው አቻቸው ዢ ጂንፒንግ ጋር…

የክልሉን ህዝብ ጥያቄ መፍታት የሚያስችል አሰራር ለመፍጠር እየተሰራ ነው-አቶ ጥላሁን ከበደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ክልላዊ ራዕይ እውን ለማድረግ የተግባርና የአስተሳሰብ አንድነት በመፍጠር የህዝባችንን ጥያቄ መፍታት የሚያስችል አሰራር ለመፍጠር እየሰራን ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የከፍተኛ…

8ኛው አመታዊ የምርምር አውደጥናት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 8ኛውን አመታዊ የምርምር አውደጥናት እያካሄደ ነው፡፡ "ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ" ለኢንዱስትሪ በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው አውደጥናቱ በዋናነት ለኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ ግብዓት ይሆናል ተብሏል።…

የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ማስተግበሪያ ፍኖተ-ካርታ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ማስተግበሪያ ፍኖተ-ካርታ እየተዘጋጀ መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በአዲስ አበባ እና በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ከተሞች ከ80 በላይ የግብዓት ማሰባሰቢያ የምክክር መድረኮች የተገኙ ሀሳቦችን መሰረት በማድረግ…

ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ በአዘርባጃን ‘አላት’ የተሰኘ ነጻ የኢኮኖሚክ ዞንን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስር ተመስገን ጥሩነህ እና ልዑካቸው በአዘርባጃን 'አላት' የተሰኘ ነጻ የኢኮኖሚክ ዞንን ጎብኝተዋል፡፡ አላት' ነጻ የኢኮኖሚክ ዞን የአዘርባጃን መንግስት የኢኮኖሚ ፕሮግራሞች ውስጥ አንዱና ዋናው ሲሆን÷ ተኪና ለዓለም አቀፍ ገበያ…

በሳዑዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 217 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 217 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ለተመላሽ ዜጎች አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር እንዲቀላቀሉ እየተሰራ መሆኑም…