Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ መሪዎች በመዲናዋ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ መሪዎች በአዲስ አበባ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ፡፡ የአፍሪካ መሪዎች የትውልድ ግንባታ ስራዎችን ጨምሮ በአዲስ አበባ በተሰሩ ዋና ዋና የልማት ስራዎች ዙሪያ ልምድ ለመካፈል አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡…

በአፍጋኒስታን በጎርፍ አደጋ ከ300 በላይ ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍጋኒስታን ከወትሮው በተለየ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ ከ300 በላይ ሰዎችን ሕይወት መንጠቁ ተሰምቷል፡፡ በአየር ንብረት ለውጥ የመጣ ነው የተባለው ይህ የጎርፍ አደጋ ከ1 ሺህ በላይ ቤቶችን እንዳወደመም የተባበሩት መንግስታት…

ማንቼስተር ሲቲ ፉልሃምን በማሸነፍ የዋንጫ ግስጋሴውን አጠናክሯል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ ፉልሃምን 4 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የማንቼስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ግቫርዲዮል (2)፣ ፎደን እና አልቫሬዝ አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም ማንቼስተር ሲቲ 85 ነጥቦችን በመሰብሰብ የሊጉን…

ሶማሌ ክልል 362 ትራክተሮችን ለአርሶ አደሮች በብድር ሊሰጥ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ግብርና እና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ለአርሶ አደሮች በብድር የሚሰጣቸውን 362 በላይ ትራክተሮች ጅግጅጋ ማስገባቱን አስታወቀ፡፡ ይህም ቢሮው ላለፉት አራት ዓመታት ሲያካሂድ የቆየው የግብርና ምርትና ምርታማነት የማሳደግ መርሐ-ግብር አካል…

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የአረጋውያን ማዕከል አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቦንጋ ዩኒቨርሲቲው በ21 ሚሊየን ብር ወጪ ያስገነባውን የአረጋውያን ማዕከል አስመረቀ። ማዕከሉ 104 ጧሪና ደጋፊ የሌላቸው አረጋውያንን የሚይዝ ሲሆን፤ ከዳያስፖራዎች፣ የግንባታ ተቋራጮች፣ ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ከውስጥ ገቢ በተገኘ ገንዘብ…

የነዳጅ እጥረት በሚፈጥሩ ማደያዎች ላይ እርምጃ መውሰድ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰው ሰራሽ የነዳጅ እጥረት እንዲፈጠር በሚያደርጉ ነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ መውሰድ የሚያስችል አዋጅ መዘጋጀቱን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሰሃረላ አብዱላሂ÷ በኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ የነዳጅ እጥረት…

ቃኘው ሻለቃ በኮሪያ የፈፀመው ገድል ኢትዮጵያ ለዓለም ሰላም መረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው – አምባሳደር ታዬ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኮሪያ ሰላም ማስከበር የተሰማራው የቃኘው ሻለቃ ጦር የፈፀመው ገድል ኢትዮጵያ ለዓለም ሰላም መረጋገጥ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳየ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ። የኢትዮጵያ ኮርያ ዘማቾች ማኅበር ኢትዮጵያ ለሰላም…

አጋር ድርጅቶች ፕሮግራሞቻቸውን ከጤና ሚኒስቴር ዕቅዶች ጋር በማጣጣም እንዲተገብሩ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አጋር ድርጅቶች ፕሮግራሞቻቸውን ከጤና ሚኒስቴር እቅዶች ጋር በማጣጣም እንዲተገብሩ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የጤና ሚኒስቴር አጋር ድርጅቶች ተወካዮች ከጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና ከሌሎች የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ…

የሕግ ማስከበሩና የሰብዓዊ መብት አያያዙ በመርህ ላይ የተመሠረተ ነው – መርማሪ ቦርዱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕግ ማስከበሩ እና የሰብዓዊ መብት አያያዙ በመርህ ላይ የተመሠረተ ነው ሲል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም መርማሪ ቦርድ አስታወቀ፡፡ የቦርዱ አባላት በአማራ ክልል በሰሜን ምዕራብ ኮማንድፖስት ሥር በጎንደር ከተማ በሚገኘው ዘጠነኛ ፖሊስ ጣቢያ…