Fana: At a Speed of Life!

የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ዝቅተኛ የተከፈለ ካፒታል መጠን ወደ 75 ሚሊየን አደገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን ዝቅተኛ የተከፈለ ካፒታል መጠን ከ50 ሚሊየን ወደ 75 ሚሊየን አሳደገ። ባንኩ ከዚህ ውሳኔ የደረሰው ወቅታዊውን ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታ እና የተቋማቱን አቅም አገናዝቦ መሆኑ ተገልጿል፡፡…

የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ትርፋማነት አስተዋጽኦ ማድረጉ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርሙ በተሰራ ስራ በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ስር የሚገኙ ተቋማት ከኪሳራ እንዲወጡ እና ትርፋማ እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉ ተገለፀ፡፡ በበጀት አመቱ ስድስት ወራት ብቻ በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና…

የሩሲያ ኩባንያዎች በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጠና በተሽከርካሪ ምርት ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ገለፁ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍቢ ሲ) ከሩሲያ የላዳ እና ጋዝ ግሩፕ መኪና አምራች ኩባንያዎች የመጡ ተወካዮች ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ሽፈራው ሰለሞን ጋር ተወያዩ፡፡ ለተወካዮቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያለውን ምቹ…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለቀድሞው የዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊ ምስጋና አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለቀድሞው የዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊ ምስጋና አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ዋና ዳይሬክተሩ በሃላፊነት ጊዜያቸው ላበረከቱት…

የኤርትራ ልዑክ በማዕድን ዘርፍ የተሰሩ የሪፎርም ሥራዎችን ጎበኘ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀነራል አብርሃ ካሳ የተመራው የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና ከፍተኛ መኮንኖች ልዑክ የማዕድን ሚኒስቴር የሠራቸውን የሪፎርም ሥራዎች ጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱ ወቅትም በማዕድን ዘርፍ የተሠሩ የሪፎርም ሥራዎችና የወደፊት ዕቅዶች ለልዑካን ቡድኑ አባላት…

“ጉዳይ ለማሥፈፀም ቢጫ ትኬት ቁረጡ” በማለት ሲያታልሉ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)"ጉዳይ ለማሥፈፀም ቢጫ ትኬት ቁረጡ” በማለት በተለያዩ አካባቢዎች በተሽከርካሪ እየተንቀሳቀሱ የማታለል ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። ተጠርጣሪዎቹ ወንጀሉን የሚፈፅሙት የኢሚግሬሽን፣…

በአቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ ልዑክ በጅማ ዞን ጉብኝት አደረገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የተመራ ልዑክ በጅማ ዞን የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎበኘ፡፡ ልዑኩ በጉብኝቱ÷ በስንዴ፣ ሙዝ፣ የሻይ ቅጠል፣ አቮካዶ እና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ልማት ላይ የተጀመሩ ስራዎችን ተመልክቷል፡፡ በጉብኝቱ…

በአዲስ አበባ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ለ3ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጎዳና ላይ ኢፍጣር የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 30 ቀን ለ3ኛ ጊዜ እንደሚካሄድ ተገለጸ። የጎዳና ላይ ኢፍጣሩ “ኢፍጣራችን ለወገናችን” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንደሚካሄድም ተጠቁሟል፡፡ ረመዳን የአብሮነት ፣ የመረዳዳት…

ኢትዮጵያ ከኢጋድ ጋር በትብብር ለመሥራት ያላትን ቁርጠኝነት አረጋገጠች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ በቀጣናዊ ጉዳዮች ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ጋር በትብብር ለመሥራት ያላትን ቁርጠኝነት አረጋገጠች፡፡ በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ እንዲሁም በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምሥጋኑ አርጋ…

በመዲናዋ በ317 ቦታዎች የአደጋ ተጋላጭነት ስጋት መኖሩ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በ180 ቦታዎች የጎርፍ አደጋ፣ በ104 ቦታዎች የመሬት መንሸራተት እንዲሁም በ33 ቦታዎች የትራፊክ አደጋ ተጋላጭነት እንዳለ የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ሰሞኑን የዝናብ ወቅት በመሆኑ እና መጪው…