Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ቱርክን በተለያዩ ዘርፎች በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያና ቱርክን በንግድ፣ በጤና፣ በኢንቨስትመንት፣ በባህል እንዲሁም በቴክኖሎጂ ሽግግር በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተጠቆመ። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት ቋሚ ቆሚቴ ሰብሳቢ ዲማ ነገዎ (ዶ/ር)…

የአፍሪካ ቱሪዝም ሚኒስትሮች ለዘላቂ ቱሪዝም ልማት እንዲሰሩ ጋና ጥሪ አቀረበች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ቱሪዝም ሚኒስትሮች ለአህጉሩ ዘላቂ ቱሪዝም ልማት እንዲሰሩ የጋና ቱሪዝም፣ ኪነ-ጥበብና ባህል ሚኒስትር ኢብራሂም መሀመድ አዋል (ዶ/ር) ጥሪ አቅርበዋል፡፡   የአፍሪካ ቱሪዝም ሚኒስትሮች አካባቢን ለመጠበቅ እና…

በተፋሰስ አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ሊፈጠር ከሚችል ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊጠነቀቁ ይገባል ተባለ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 26 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በነሐሴ ወር በኢትዮጵያ ተፋሰሶች ላይ የሚኖረውን ከፍተኛ የዝናብ ስርጭት ተከትሎ ሊፈጠር ከሚችል ቅጽበታዊ ጎርፍ መጠንቀቅ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አሳሰበ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ በመጪው ነሐሴ ወር በሰሜን…

የመዲናዋ ነዋሪዎች የቤት ጣሪያና ግድግዳ ግብር ክፍያቸውን እስከ ነሐሴ 30 እንዲያጠናቅቁ ማሳሰቢያ ተሠጠ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የመዲናዋ ነዋሪዎች የቤት ጣሪያና ግድግዳ ግብር ክፍያቸውን እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ እንዲያጠናቅቁ አሳሰበ። የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አደም ኑሪ ፥ በቤት ወይም በከተማ ቦታ ኪራይና የቤት…

በቤጂንግ በ140 ዓመታት ታሪክ ውስጥ አጋጥሞ የማያውቅ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ጣለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና ቤጂንግ ከፈረንጆቹ ሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 2 ቀን 2023 በ140 ዓመታት ታሪክ ውስጥ አጋጥሞ የማያውቅ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ መጣሉ ተገለጸ። ከተማዋ በቅዳሜ እና ረቡዕ ጠዋት መካከል 744 ነጥብ 8 ሚሊ ሜትር ዝናብ መመዝገቡን…

የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እስከ ነሀሴ 30 ድረስ በነበረበት እንደሚቀጥል ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሁሉም ነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ በሀምሌ ወር ሲሸጥ በነበረው ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በመጪዎቹ ጊዜያት የአለም የነዳጅ ገበያን መነሻ በማድረግ…

የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት በጥቃቅንና መካከለኛ ኢንዱስትሪ የተሰማሩ ሴት አምራቾችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጀይ ባንጋ በሁለተኛው ቀን የኢትዮጵያ ቆይታቸው በጥቃቅንና መካከለኛ ኢንደዱስትሪ የተሰማሩ ሴት አምራቾችን ጎብኝተዋል። በኢትዮጵያ መንግስትና የዓለም ባንክ ድጋፍ በሚንቀሳቀሰው የሴቶች ኢንተርፕሩነር ሺፕ ልማት ፕሮግራም…

በአማራ ክልል ህግን ለማስከበር በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ህዝቡ የተለመደ ትብብሩን እንዲያሳይ ተጠየቀ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 26 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፀጥታ አካላት በክልሉ ህግን ለማስከበር በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ሁሉ ህዝቡ ድጋፍ በማድረግ የተለመደ ትብብሩን እንዲያሳይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ላይ…

አቶ ማሞ ምህረቱ ከአሜሪካ ግምጃ ቤት ምክትል ረዳት ፀሐፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 26 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ከአሜሪካ ግምጃ ቤት ምክትል ረዳት ፀሐፊ ኤሪክ ሜየር ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ-ግብር ላይ ያተኮረ መሆኑን ባንኩ በትዊተር ገጹ ባሰፈረው መረጃ አመላክቷል።…

የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድርን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል ጌዴኦ ዞን የሚገኘውን የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሣይንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ለማስመዝገብ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ገለጸ፡፡ የዞኑ ባህል እና ቱሪዝም መምሪያ…