Fana: At a Speed of Life!

በትግራይ ክልል የጤና ተቋማትን መልሶ ለማደራጀት የሚያስችል ጉብኝት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል የጤና ሥራዎችን ለማየት እና ተቋማቱን መልሶ ለማቋቋም የሚያስችል ጉብኝት እየተካሄደ ነው፡፡ ከጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የተውጣጡት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ልዑካን ቡድን በጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ መሪነት በትግራይ ክልል…

ኢትዮጵያ በተመድ የሕዝብና ዕድገት ኮሚሽን ጉባዔ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በኒውዮርክ እየተካሄደ ባለው በተባበሩት መንግስታት የሕዝብና ዕድገት ኮሚሽን 56ተኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው፡፡ ጉባዔው “ሕዝብ፣ ትምህርት እና ዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ሐሳብ ነው እየተካሔደ የሚገኘው፡፡ በፕላንና ልማት…

ሀገር አቀፍ የፀረ-አደንዛዥ ዕፆች የንቅናቄ ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)''ወጣቶችን ከአደንዛዥ ዕፆች  እና መጤ ልማዳዊ ድርጊቶች እንታደግ'' በሚል ቃል ሀገር አቀፍ የፀረ-አደንዛዥ ዕፆች የንቅናቄ ማስጀመሪያ መረሃ ግብር  እየተካሄደ ነው። የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)  በመርሃ ግብሩ…

ሩሲያ አህጉር አቋራጭ የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አደረገች

ተተኩሶአዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ አህጉር አቋራጭ የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራ በተሳካ ሁኔታ ማከናወኗን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚሳኤሉ ከደቡባዊ ሩሲያ ካፑስቲን ያር ተተኩሶ በካዛኪስታን ሳሪ ሻጋን በሚገኘው ክልል ውስጥ በታቀደለት መልኩ ማረፉ ተገልጿል።…

ኢትዮጵያ ሀገር-በቀል ኢኮኖሚ ላይ በትኩረት እንደምትሠራ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ ሀገር-በቀል ኢኮኖሚ ላይ በትኩረት እንደምትሠራ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ አስታወቁ። ሚኒስትሩ “ከዕዳ መውጣት ፣ ዕድገት ማስመዝገብ” በሚል መሪ ቃል አሜሪካ በተዘጋጀው በዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ መድረክ የፓናል ውይይት ላይ…

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሯ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው የሁለት ቀን ቆይታ ከመንግስት እና ከአፍሪካ ሕብረት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል። ጉብኝቱ…

የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ሕብረተሰቡ ከግብይት መጭበርበር ሊጠነቀቅ እንደሚገባ አስገነዘበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ስልታቸውን እየቀያየሩ በበዓል ሰሞን ከሚፈጸሙ የግብይት መጭበርበሮች ሕብረተሰቡ እንዲጠነቀቅ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት አሳሰበ፡፡ የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን እና ሕዝብ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ እንዳለ አሰፋ እንዳሉት÷ በርካቶች እንደአቅማቸው…

በበዓል ሰሞን አደጋ እንዳይከሰት ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ተጠየቀ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 4 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከበዓላት ጋር በተያያዘ አደጋዎች እንዳይከሰቱ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ፡፡ በበዓላት ወቅት እሳት እና የኤሌክትሪክ ኃይል በስፋት ጥቅም ላይ ስለሚውሉ ይህን ተከትሎ በመጪው የትንሳዔ በዓል…

በብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር የተመራ ልዑክ ከአፋር ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያየ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በብሄራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ የተመራ ልዑክ በዛሬው ዕለት ከአፋር ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር ምክክር አካሂዷል። በመድረኩ ላይ ከመንግስት ጋር በተደረገ የሰላም ስምምነት መሰረት ትጥቃቸውን የፈቱ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ…