Fana: At a Speed of Life!

ከ1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የአማራ ሕዝብ ሙዚየም ግንባታ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 7፣2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል መንግሥት ከ1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የአማራን ሕዝብ ሙዚየም ማስገንባት መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ሙዚየሙ የአማራን ሕዝብ ቅርስ፣ ታሪክና ባሕሉን ለማስቀመጥ ከማገልገል ባለፈ አንዱ የቱሪዝም መዳረሻ እንደሚሆን ታምኖበታል፡፡…

ኢትዮጵያ የቪዛ ስርዓቷን ለአፍሪካዊያን የበለጠ በማቅለል እመርታ ማሳየቷን የአፍሪካ ልማት ባንክ ሪፖርት አመለከተ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት ማለትም ከፈረንጆቹ 2016 እስከ 2022 ለአፍሪካዊያን የቪዛ ስርዓቷን በማቅለል በሯን ይበልጥ ክፍት በማድረግ እመርታ ማሳየቷን የአፍሪካ ልማት ባንክ ሪፖርት አመለከተ። በአፍሪካ ጥቂት አገሮች በ2016 እና 2022…

ዩዜን ቦልት የቢቢሲ ስፖርት የሕይወት ዘመን ስኬታማ ሰው ሽልማትን አሸንፈ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 7፣2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጃማይካዊው አትሌት ዩዜን ቦልት የቢ ቢ ሲ ስፖርት የሕይወት ዘመን ስኬታማ ሰው ሽልማትን አሸንፏል፡፡ ቦልት ከሽልማቱ በኋላ ለቢቢሲ ስፖርት በሰጠው አስተያየት "ጠንክረህ ከሰራህ የምትፈልገውን ነገር እንደምታገኝ  እኔ ኅያው ምስክር ነኝ" ሲል…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዋሺንግተን ዲሲ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ኮሙዩኒቲ አባላት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ በሚገኘው የአሜሪካ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸው…

የባህልና ቱሪዝም ዘርፉን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመን ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የባህልና ቱሪዝም ዘርፉን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ማዘመን የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ፡፡ ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ እና የአማራ ብሔራዊ ክልል የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ጣሂር መሃመድ ተፈራርመውታል፡፡…

2ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21 ቀን በዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁለተኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21ቀን 2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ፡፡   በፈተናው የሚሳተፉትም የመጀመሪያ ዙር ፈተናን በወሊድ ወይም…

ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ የአፍሪካ ሰብዓዊ ኤጀንሲን ለማቋቋም ስላለው ጥረት መከሩ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ የአፍሪካ ሰብዓዊ ኤጀንሲን ለማቋቋም ስላለው ጥረት ለአፍሪካ ኅብረት እና ለተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዳይሬክተር ጋር መክረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቷ ÷ በአፍሪካ የሥነ-ሕዝብ ዕድገት ፣ እንዲሁም በትምህርትና በጤናው…