Fana: At a Speed of Life!

በደቡብ ክልል በህገ-ወጥ ንግድ ተሰማርተዋል በተባሉ ከ23 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወሰደ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል በህገ-ወጥ ንግድ ላይ ተሰማርተዋል በተባሉ 23 ሺህ 303 ነጋዴዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የደቡብ ክልል የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የደቡብ ክልል ምክር ቤት የከተማ ልማትና መሰረተ-ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን…

የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭትን በሚያስተጓጉሉ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ባለስልጣኑ አስጠነቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭትን በሚያስተጓጉሉ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን አስጠነቀቀ፡፡ በቀን ከዘጠኝ ሚሊየን ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ እየገባ ቢሆንም ተጠቃሚው ዘንድ በወቅቱ…

የግብርና ሜካናይዜሽን የልኅቀት ማዕከልን ለማቀቋቋም ከደቡብ ኮሪያ ጋር እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያን ግብርና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና ሜካናይዜሽን ለመደገፍ የሚያስችል የልኅቀት ማዕከል ለመገንባት ከደቡብ ኮሪያ መንግስት ጋር በትብብር እየተሠራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያን የግብርና ሜካናይዜሽን የልኅቀት ማዕከል…

በአዲስ አበባ ከተማ ከመጪው ሰኔ 27 እስከ 29 የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይሰጣል

አዲ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ሦስት ቀናት እንደሚሰጥ ተገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ…

በደቡብ ምዕራብ ክልል የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተመሰረተ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተመሰረተ፡፡ በክልላዊ የጋራ ምክር ቤት ምስረታ መርሐ ግብሩ ላይ÷ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ፣ ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ፣ ብልጽግና…

ኢትዮጵያ እና ሱዳን በድንበራቸው አካባቢ የተፈጠረውን ውዝግብ በውይይት እንዲፈቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና ኢጋድ ጠየቁ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ሱዳን በድንበራቸው አካባቢ የተፈጠረውን  ውዝግብ በውይይት እንዲፈቱ የአፍሪካ ህብረት እና ኢጋድ ጠየቁ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት የኢትዮጵያ እና ሱዳን ወታደራዊ ውጥረት ኮሚሽኑን እንደሚያሳስበው ገልፀዋል፡፡…

ከጀርመን መንግስት የ32 ሚሊየን ዩሮ በላይ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጀርመን መንግስት የ32 ሚሊየን ዩሮ በላይ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል የፕሮግራም ስምምነት መፈረሙን የስራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡   የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ከጀርመን የልማት ባንክ የአፍሪካ ህብረትና…

ኩባ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር እንደምትፈልግ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኩባ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ማጠናከር እንደምትፈልግ አስታውቃለች፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ ከኩባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሩኖ ሮድሪጌዝ ፓሪላ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ የኩባ…

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባህሬን አቋርጦት የነበረውን በረራ ሊጀምር ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባህሬን አቋርጦት የነበረውን በረራ በዚህ ሣምንት መጨረሻ እንደሚጀምር አስታውቋል፡፡ የኢፌዲሪ ቆንስላ ጄኔራል ጽሕፈት ቤት መሪ አምባሳደር አወል ወግሪስ በባህሬን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ወኪል አቶ…

በመዲናዋ የሸገር ድጋፍ ሰጪ አውቶቡሶች ውል ለተጨማሪ ስድስት ወራት ተራዘመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣2014(ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ የሸገር ድጋፍ ሰጪ አውቶቡሶችን ውል ለተጨማሪ ስድስት ወራት አራዘመ፡፡ ውሉ ከመጋቢት 4/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለስድስት ወራት እስከ መስከረም 2/2015 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡ በመዲናዋ ድጋፍ ሰጪ…