Fana: At a Speed of Life!

የኢድ-አልፈጥር በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር ተከብሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ የጋራ ግብረ ኃይሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ተልዕኮውን በቁርጠኝነት እየተወጣ እንደሚገኝ…

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢድ-አልፈጥር በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር ተከብሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ የጋራ ግብረ ኃይሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ተልዕኮውን በቁርጠኝነት እየተወጣ እንደሚገኝ አስታወቀ። የጋራ ግብረ ኃይሉ የኢድ-አልፈጥር በዓል የመልካም ምኞት መግለጫ…

የሴቶች የኢኮኖሚ ብቃት ፎረም በብሔራዊ ደረጃ ተቋቋመ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የሴቶችን የኢኮኖሚ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተቀናጀ መልኩ ለመስራት የሚያስችል የሴቶች የኢኮኖሚ ብቃት ፎረም ዛሬ በብሔራዊ ደረጃ ተቋቁሟል፡፡ በፎረሙ መመስረቻ መርሃ ግብር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ አለሚቱ ኦሞድ…

የሃይማኖት ልዩነት አጥር ሆኖብን አያውቅም – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)  የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ትላንት በመዲናዋ የተካሄደው ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። ከንቲባ አዳነች በምስጋና መልዕክቸው “የሃይማኖት ልዩነት አጥር ሆኖብን…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መጪውን የኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ በወልድያ የሚገኙትን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ዕዞች ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መጪውን የኢድ አልፈጥር በአል ምክንያት በማድረግ በሰሜን ወሎ ዞን ወልድያ ከተማ የሚገኙትን የሀገር መከላከያ ሠራዊትን የደቡብ፣ ምሥራቅ፣ 6ኛ እና 8ኛ ዕዞችን ጎብኝተዋል።   በወልድያ…

አሜሪካ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ሰላም እንዲመጣና በግጭት የተጎዱ ዜጎችን ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን ገለፀች

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)  የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በቢሯቸው በኩል በኢትዮጵያ ግጭቶችን ለማስቆም እየተካሄዱ የሚገኙ ተግባራዊ ስራዎችን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል። አሸባሪው ህወሃት በፈጠረው ጦርነትና በወረራ በያዛቸው አካባቢዎችን እንዲሁም…

“ኢትዮጵያ ታምርት ” በሚል መሪ ቃል የኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት አምራቾችን አቅም የማሳደገያ ንቅናቄ መድረክ  እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)  "ኢትዮጵያ ታምርት " በሚል መሪ ቃል የአዲስ አበባ የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት አምራቾችን አቅም የማሳደገያ የምክክርና ንቅናቄ መድረክ  እየተካሄደ ነው ። መድረኩን በይፋ ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች…

የዓለም የሠራተኞች ቀን በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የሠራተኞች ቀን በኢትዮጵያ ለ47ኛ ጊዜ እየተከበረ ነው። የሠራተኞች ቀን “ሜይዴይ” የዓለም ሠራተኞች ለዘመናት ያካሄዱትን ታሪካዊ ትግል፣ ሠራተኞችና ንቅናቄዎቻቸው ያስገኟቸው ድሎች፣ የከፈሏቸው መስዋትነቶች በጋራ የሚዘክሩበትና…

የዓለም የምግብ ፕሮግራም በትግራይ ክልል በከባድ ሁኔታ ውስጥም እያደረገ ያለው የሰብአዊ እርዳታ የሚያስመሰግን ነው – አቶ ደመቀ መኮንን

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን በቅርቡ አዲስ ከተሾሙት የዓለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተጠሪ ዳይሬክተር ክላዉድ ጂቢዳር ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። አቶ ደመቀ የዓለም የምግብ…

በአዲስ አበባ የተዘጋጀው የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐ ግብር በሠላም መጠናቀቁን የፀጥታና ደህንነት ግብረ ኃይል አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተዘጋጀው የጎዳና ላይ ታላቅ የኢፍጣር መርሓ ግብር ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር መጠናቀቁን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡ ለመርሓ ግብሩ በሠላም መጠናቀቅ አስተዋፅኦ…

ባለሥልጣኑ የጥላቻ ንግግር በሚያሠራጩ የመገናኛ ብዙኃን ላይ እርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጥላቻ ንግግር በሚያሠራጩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ እንዳለበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳሰበ። በምክር ቤቱ የሕግ፣ ፍትሕ እና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ…