Fana: At a Speed of Life!

የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ ዛሬ ይመረቃል

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 29፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ ቁጥር አንድ የ15ቀን የሙከራ የምርት ጊዜውን በማጠናቀቅ ዛሬ ይመረቃል። ፋብሪካው በቀን 12 ሺህ ቶን ስኳር ማምረት የሚችል ሲሆን በዓመት 2 ሚለየን 372 ሺህ ቶን ስኳር የማምረት…

ለስምንት ዓመት የተጓተተው ግድብ 70 በመቶ ላይ ደረሰ – ዐቢይ አህመድ

 አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለስምንት ዓመት የተጓተተው የመገጭ ግድብ 70 በመቶ ላይ ደረሰ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፕሮጅክቱ አፈጻጸም የተሰማቸውን ደስታ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል። የግድቡ ግንባታ እጅግ…

ለመኸር እርሻ የሚውል ከ12 ሚሊየን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች እየተከፋፈለ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ2013 እና 2014 የምርት ዘመን ለመኸር እርሻ የሚውል ከ12 ሚሊየን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች እየተከፋፈለ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን አስታወቀ። ኮርፖሬሽኑ ለ2013/14 የምርት ዘመን ለመኸር እርሻ የሚውሉ…

የኢትዮጵያ የሠላም ማስከበር ተልዕኮ ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተለያዩ ሃገሮች ወታደራዊ አታሼዎች ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሠላም ማስከበር ተልዕኮ ውስጥ የምታደርገው ተሳትፎ የሚደነቅና ሊቀጥል የሚገባው ተግባር መሆኑን የተለያዩ ሃገሮች ወታደራዊ አታሼዎች ገለጹ። መቀመጫቸውን በኢትዮጵያ ያደረጉ የተለያዩ ሃገሮች ወታደራዊ…

2 ሚለየን 372 ሺህ ቶን ስኳር የማምረት አቅም ያለው የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ በነገው ዕለት ይመረቃል

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በግንባታ መዘግየትና የጥራት ችግር ውስጥ የነበረው የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ ቁጥር አንድ  የ15ቀን የሙከራ የምርት ጊዜውን በማጠናቀቅ በነገው ዕለት ይመረቃል። ፋብሪካው 2 ሚለየን 372 ሺህ ቶን ስኳር የማምረት አቅም…

በሀረሪ ክልል “ህገ መንግስታዊ መብቶች የህገ መንግስታዊ ዋስትና አላቸው” በሚል መሪ ቃል ሲምፖዚየም ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በሀረሪ ክልል በዛሬው እለት "ህገ መንግስታዊ መብቶች የህገ መንግስታዊ ዋስትና አላቸው " በሚል መሪ ቃል ሲምፖዚየም ተካሂዷል፡፡ ሲምፖዚየሙን በንግግር የከፈቱት የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እንደተናገሩት፥ ባለፉት ሶስት አመታት…

የደቡብ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መስጫ ጊዜ ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ክልላዊ የ8ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 28 እስከ 30 2013 ዓ.ም እንደሚሰጥ የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል፡፡ የቢሮ ምክትል ኃላፊና የመማር ማስተማር ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ገለቦ ጎልቶሞ ፥ ቢሮው አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ…

የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በርካታ መምህራን እየሰለጠኑ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን የመምህራን አቅም በማሳደግ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በርካታ መምህራን በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ደረጃ በሃገር ውስጥና በውጪ እየሰለጠኑ እንደሚገኙ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። የጋምቤላ…

በኮምቦልቻ ከተማ ማር ከባዕድ ነገር ጋር ቀላቅሎ ሲያዘጋጅ የተገኘ ግለሰብ ተያዘ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኮምቦልቻ ከተማ በመኖሪያ ቤቱ ማር ከባዕድ ነገር ጋር በመቀላቀል ለሽያጭ ሲያዘጋጅ የተገኘ ግለሰብ በህብረተሰብ ጥቆማ እጅ ከፈንጅ መያዙን ፖሊስ አስታወቀ። በከተማ አስተዳደሩ የበርበሬ ወንዝ ፖሊስ ጣቢያ ሃላፊ ኮማንደር ወንድዬ በላይ…

የኢትዮጵያና ኬንያ ግንኙነት መጠናከር ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያና ኬንያ ግንኙነት መጠናከር ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ጉልህ ሚና እንዳለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ተወካይ ገለጹ፡፡ በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም…