Fana: At a Speed of Life!

የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 23 እና 24 ተከብሮ ይውላል- አባ ገዳዎች

አዲስ አበባ፡ መስከረም 6 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 23 እና 24 ተከብሮ እንደሚውል አባገዳዎች ዛሬ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በዚህም የሆራ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል መስከረም 23 በአዲስ አበባ ፣ የሆራ አርሰዲ ኢሬቻ በዓል ደግሞ መስከረም 24 ቀን 2013…

የጤና ሚኒስቴር ትምህርት ለመጀመር የሚስችል ሁኔታ መኖሩን ሲያረጋጥልን ትምህርት እንጀምራለን – የትምህርት ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጤና ሚኒስቴር ትምህርት ለመጀመር የሚስችል ሁኔታ መኖሩን ሲያረጋጥልን ትምህርት እንጀምራለን ሲሉ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ አስታወቁ፡፡ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ያለበት ደረጃ ተገምግሞ ትምህርት ለመጀመር የሚያስችል…

በአዲስ አበባ የ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመንን ለማስጀመር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመንን ለማስጀመር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የከተማዋ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የኮሮና ቫይረስን በመከላከል ትምህርትን በመደበኛ መልኩ ለመጀመር ዝግጅት…

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በኢትዮጵያ የስራ ዘመናቸዉን ያጠናቀቁ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችን አሰናበቱ

አዲስ አበባ፡ መስከረም 6 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በኢትዮጵያ የስራ ዘመናቸዉን ያጠናቀቁ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችን አሰናብተዋል። ፕሬዚዳንቷ ያሰናበቷቸው የስራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ የስዊዘርላንድ ፣ የኢራን እና የቻይና አምባሳደሮችን መሆኑ ተገልጿል። በዚሁ…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ተያዘ

አዲስ አበባ፡ መስከረም 6 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ መያዙን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡   በክልሉ በሚገኙ 4 የተለያዩ ኬላዎች በተደረገ ፍተሻ 2 ሚሊየን 370 ሺህ ብር መያዙንን…

በአፋር ክልል በጎርፍ አደጋ ለተፈናቀሉ ዜጎች የተለያዩ ድርጅቶች ድጋፍ እያደረጉ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፡ መስከረም 6 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአፋር ክልል በጎርፍ አደጋ ለተፈናቀሉ ዜጎች የተለያዩ ድርጅቶች ድጋፍ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል። በመንግስትና በግል ተቋምና ግለሰቦች ከሚደረገው ድጋፍ በተጓዳኝ የተራድኦ ድርጅቶችም እየረዱ መሆኑ ነው የተመላከተው ። በዛሬው እለትም…

274 ኢትዮጵያውያን ከሳኡዲ አረቢያ ወደ አገራቸወ ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሳኡዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ በተለያዩ ችግር ውስጥ ይኖሩ የነበሩ 274 ኢትዮጵያውያን ዜጎች ዛሬ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። ኢትዮጵያውያን ዜጎች ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል…