Fana: At a Speed of Life!

እስራኤል በሀውቲ አማፂያን ወታደራዊ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ፈፀመች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) እስራኤል በየመን ዋና ከተማ ሰነዓ በሚገኙት የሀውቲ አማፂያን ወታደራዊ መሰረተ ልማቶች ላይ መጠነ ሰፊ የአየር ጥቃት መፈፀሟ ተሰምቷል፡፡ የአየር ጥቃቱ የሀውቲ አማፂያን መሪ የሆኑት አቡድል ማሊክ አል ሀውቲ በቴሌቪዥን ንግግር እያደረጉ ባለበት…

ኢትዮጵያ ለምሥራቅ አፍሪካ ሰላምና ደኀንነት መጠበቅ ያላትን ሚና እንደምታጠናክር ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለምሥራቅ አፍሪካ ሰላም እና ደኀንነት መጠበቅ ያላትን ሚና አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለጹ፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዘጋጅነት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለነባር ዲፕሎማቶችና…

የቅዱስ ገብርዔል ዓመታዊ የንግስ በዓል በድምቀት ለማክበር ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ታሕሣሥ 19 የሚከበረውን የቁልቢ እና የሐዋሳ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ፡፡ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ÷…

መረጃዎች በቴሌግራም እየተመዘበሩ ነው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በዛሬው ዕለት በቴሌግራም መረጃዎች እየተመዘበሩ በመሆኑ ተጠቃሚዎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳሰበ፡፡ አስተዳደሩ እንዳለው ከዛሬ ጀምሮ ብዙ የቴሌግራም አካውንቶች በተጠቀሰው የማስገሪያ (ፊሺንግ…

በቦክሲንግ ዴይ የመክፈቻ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ነጥብ ጣለ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በገና በዓል ሰሞን(ቦክሲንግ ዴይ) የመክፈቻ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ኤቨርተንን አስተናግዶ 1 አቻ ተለያይቷል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ከ30 በኢቲሃድ በተደረገው ጨዋታ በርናርዶ ሲልቫ ለማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም ኢልማን ኒዲያየ ለኤቨርተን ጎሎችን…

በኢትዮጵያ ክትባት ለማምረት የአዋጭነት ጥናት ሊካሄድ ነው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ክትባት ለማምረት የአዋጭነት ጥናት ለማድረግ የጤና ሚኒስቴር እና ቴክኢንቬሽን ላይፍኬር ኩባንያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የመግባቢያ ሰነዱ መፈረም በኢትዮጵያ ክትባት ለማምረት የሚረዳ ትልቅ…

ለቢሾፍቱ እድገት የአየር ኃይሉ አስተዋፅኦ ተጠናክሮ ይቀጥላል – ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለቢሾፍቱ ከተማ ለውጥና እድገት የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስተዋፅኦ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአየር ኃይሉ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ፡፡ ሌተናል ጄኔራል ይልማ ለከተማዋ ኮሪደር ልማት ተቋሙ ከባለሀብቶችና የልማት አጋር ግለሰቦች…

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ስርዓት ግንባታ ሂደት ተቀራርቦ የመስራትና የመነጋገር ባህልን ያመጣ ነው – ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)በኢትዮጵያ የፖለቲካ ስርዓት ግንባታ ሂደት ተቀራርቦ የመስራትና በሃሳብ የበላይነት የመነጋገር ባህልን ያመጣ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)…

ብልፅግና ፓርቲ ዕዳ ሳይሆን ምንዳ እናወርሳለን ብሎ የገባውን ቃል በተግባር እያረጋገጠ ነው – አብርሃም በላይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ብልፅግና ፓርቲ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በመፈጸም ዕዳ ሳይሆን ምንዳ እናወርሳለን ብሎ የገባውን ቃል በተግባር እያረጋገጠ ነው ሲሉ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ አብርሃም በላይ…

የተባበሩት መንግስታት የሳይበር ወንጀሎችን አስመልክቶ ስምምነት አፀደቀ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የተባበሩት መንግስታት የሳይበር ወንጀልን ለመከላከልና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለመፍጠር የሚያስችል ስምምነት ማጽደቁን አስታወቀ፡፡ ስምምነቱ በተባበሩት መንግስታት አባል ሀገራት መካከል በ20 ዓመታት ውስጥ የተደረገ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ…