በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉና ምርት ያከማቹ 1 ሺህ 435 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ዋጋ በጨመሩ እና ምርትን ባከማቹ 1 ሺህ 435 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ለሸማቾች፣ ለንግድ ማህበረሰብ ጨምሮ…