Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ኪርጊስታን ኢኮኖሚያዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከኪርጊስታን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አሲዬን ኢሳዬቭ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በኢትዮጵያና ኪርጊስታን መካከል ያለውን ኢኮኖሚናዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡…

በትምሕርቱ ዘርፍ ለኢትዮጵያ የማደርገው ድጋፍ ይቀጥላል- ጀርመን

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጀርመን በኢትዮጵያ በተለያየ ምክንያት የወደሙ ትምሕርት ቤቶችን መገንባትን ጨምሮ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ጥረት ድጋፏ እንደሚቀጥል አረጋገጠች፡፡ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ከሆኑት ጄንስ…

ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልካቸውን ምርቶች ለማሳደግ ያለመ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በቻይና ምክር ቤት የልማት ምርምር ማዕከል ፕሬዚዳንት ሉ ሃኦ የተመራ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በኢትዮጵያና ቻይና የንግድ ግንኙነት ዙሪያ ሰፋ ያለ ምክክር ማድረጋቸውን ካሳሁን…

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዋጋ ንረትን ከ30 በመቶ ወደ 17 በመቶ ዝቅ እንዲል አግዟል – ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የዋጋ ንረት ከነበረበት 30 በመቶ ወደ 17 በመቶ ዝቅ እንዲል አግዟል ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ÷ በጥብቅ…

ለሰላም አዎንታዊ ምላሽ የሰጡ ታጣቂዎች በሀገረ መንግስት ግንባታ እንዲሳተፉ ድጋፍ ይደረጋል – ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሰላም አዎንታዊ ምላሽ የሰጡ የታጠቁ ቡድኖች በሀገረ መንግስት ግንባታ ሥራዎች በንቃት እንዲሳተፉና የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) አረጋግጠዋል፡፡…

ክልሎች የከተራና ጥምቀት በዓልን ለማክበር መዘጋጀታቸውን አስታወቁ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጋምቤላ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የከተራና ጥምቀት በዓል ለማክበር አስፈላጊ ዝግጅት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። በጋምቤላ ክልል የከተራና ጥምቀት በዓል ያለምንም የፀጥታ ስጋት…

ኧርሊንግ ሃላንድ በማንቸስተር ሲቲ እስከ 2034 የሚያቆየውን ኮንትራት ፈረመ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የማንቸስተር ሲቲው አጥቂ ኧርሊንግ ሃላንድ በቡድኑ እስከ 2034 የሚያቆየውን ውል መፈረሙ ተገለጸ። የ24 ዓመቱ ኖርዌያዊ አጥቂ ከቅርብ ጊዜ  ወዲህ የአቋም መውረድ ማሳየቱን ተከትሎ ቡድኑን ሊለቅ ይችላል የሚል ጭምጭምታ ሲሰማ…

ጥምቀትን በጎንደር የባሕል ሳምንት ማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ ሲካሄድ የነበረው ‘ጥምቀትን በጎንደር የባሕል ሳምንት’ ማጠቃለያ መርሐ ግብር ዛሬ ተካሂዷል። የአማራ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ጸጋየ በዚህ ወቅት÷ ከተማ አስተዳደሩ በዓሉን በድምቀት ለማክበር አስፈላጊውን…

በፈጠራ የተሞላ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዕውቀት እና በፈጠራ የተሞላ ኢኮኖሚ ለመገንባት እየተሠራ ነው ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴዔታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ጋር በጋራ ለስድስት ወራት ያሰለጠናቸውን 12…

1 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል የጥጥ ምርት ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2016/17 የምርት ዘመን 1 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል የጥጥ ምርት መሰብሰቡን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። በግብርና ሚኒስቴር የጥጥ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሳምሶን አሰፋ እንደገለጹት÷ ለጥጥ ልማት እንደ ገዋኔ፣ መተማ፣ ሑመራ፣ ጋሞ፣ ጎፋ…