Fana: At a Speed of Life!

የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። መስተዳድር ምክር ቤቱ በዋናነትም ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው ለኢንቨስትመንት የተዘጋጁ መሬቶችን እንዲሁም በመልሶ ማልማት…

በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1 እስከ 4 በመሆን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንደኛ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ በበላይነት አጠናቀዋል፡፡ በውድድሩ በሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር መቅደስ ዓለምሸት 14 ደቂቃ ከ36 ሰከንድ በመግባት አሸንፋለች፡፡ አያል ዳኛቸው…

አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደግፍ  የተሻለ የስራ እድል ለመፍጠር በመስራት ላይ እንገኛለን – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አምራች ኢንዱስትሪዎችን በመደግፍ  የተሻለ የስራ እድል ለመፍጠር በመስራት ላይ እንገኛለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡ “ኢትዮጵያ-ታምርት፤ እኛም እንሸምት” በሚል መሪ ሃሰብ የተዘጋጀው የኢንዱስትሪዎች…

መከላከያ ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን በመረዳት የሀገር ደህንነትን የሚያስጠብቁ መሪ መኮንኖችን እያፈራ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) መከላከያ እንደተቋም ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን በመረዳትና በመተንተን ሀገራዊ ደህንነትን የሚያስጠብቁ መሪ መኮንኖችን እያፈራ መሆኑ ተገለፀ፡፡ የመከላከያ ዋር ኮሌጅ በሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያሰለጠናቸዉን ከፍተኛ መኮንኖች…

አትሌት መዲና ኢሳ በ5 ኪሎ ሜትር ከ20 ዓመት በታች የሩጫ ውድድር የዓለም ክብረ ወሰን ሰበረች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲዳስ ኩባንያ ባዘጋጀው አዲዜሮ የ5ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት መዲና ኢሳ ከ20 ዓመት በታች የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር አሸነፈች፡፡ የ19 ዓመቷ አትሌት መዲና ርቀቱን 14 ደቂቃ ከ38 ሰከንድ በማጠናቀቅ ነው የዓለም ክብረ ወሰንን በመስበር…

ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ አሜሪካ የቻይናን ዕድገት በበጎ ማየት እንዳለባት አስገነዘቡ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በራሷ የምትተማመን፣ ግልፅ እና የበለፀገች አሜሪካን በማየቷ ቻይና ደስ እንደሚላት ሁሉ አሜሪካም የቻይናን ዕድገት በአዎንታዊ መልኩ ማየት እንደሚጠበቅባት ፕሬዚዳንት ሺ አስገነዘቡ፡፡ ፕሬዚዳንቱ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ…

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካቢኔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካቢኔ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ካቢኔው በመጀመሪያ የተወያየው÷ የክልሉን ደረጃ የሚመጥን እና ዘመናዊ ቴክኖሎጅ ተሟቶለት በተዘጋጀው የመሥተዳድር ምክር ቤት እና…

የፍቼ ጫምባላላ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ፣ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፍቼ ጫምባላላ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉ አከባበር ላይም የፌደራል መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሲዳማ ክልልና የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ በተጨማሪም በአዲስ አበባ…

የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ከ2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተጓዦችና የጭነት አገልግሎት ከ2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ። ማኅበሩ በየቀኑ ከ7 መቶ እስከ 1ሺህ ሰዎችን የማጓጓዝ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን÷…