ስፓርት
አሌክሳንደር አርኖልድ ከልጅነት ክለቡ ጋር እንደሚለያይ አረጋግጧል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከልጅነት ክለቡ ሊቨርፑል ለመልቀቅ መወሰኑን አስታውቋል፡፡
አሌክሳንደር አርኖልድ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው መረጃ፤ ራሱን በአዲስ ክለብ እና በተለየ ቦታ ለመፈተሽ በመፈለጉ ከሊቨርፑል ለመልቀቅ መወሰኑን አስታውቋል፡፡
ወደ አዲስ ክለብ መሄዱም ያለውን ሙሉ አቅም አውጥቶ እንዲጠቀም እንደሚያስችለው ነው የገለጸው፡፡
ላሳደገው ክለብም ያለውን ክብር እና ፍቅር ገልጾ፤ ለመልቀቅ የወሰነው ከገንዘብ ጋር በተያያዘ ጉዳይ አለመሆኑን…
Read More...
ቼልሲ ከሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ በስታምፎርድ ብሪጅ ሊቨርፑልን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጠበቃል።
ለቀጣይ ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ እየተፎካከሩ የሚገኙት ሰማያዊዎቹ ምሽት 12:30 የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ካረጋገጠው ሊቨርፑል ጋር ይጫወታሉ።
በጨዋታው መጀመሪያ…
አርሰናል በበርንማውዝ ተሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በሜዳው ኤሚሬትስ ስታዲየም በርንማውዝን ያስተናገደው አርሰናል 2 ለ 1 ተሸንፏል፡፡
የበርንማውዝን የማሸነፊያ ግቦች ዲያን ሁጅሰንና ኢቫኒልሰን ሲያስቆጥሩ አርሰናልን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ዲክላን ራይስ ከመረብ አሳርፏል፡፡
ቀደም ብለው በተደረጉ…
ኢትዮጵያ መድን አርባ ምንጭ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን አርባ ምንጭ ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አለን ካይዋ እና አቡበከር ሳኒ የመድንን የማሸነፊያ ግቦች አስቆጥረዋል፡፡
የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሃዋሳ…
በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃን ያዙ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቻይና ሻንጋይ በተካሄደው የወንዶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት በሪሁ አረጋዊ አሸንፏል፡፡
አትሌቱ ርቀቱን በ12 ደቂቃ 50 ሰከንድ ከ45 ማይክሮ ሰከንድ በማጠናቀቅ ነው ቀዳሚ የሆነው፡፡
ሌላኞቹ ኢትዮጵያውያን አትሌት ኩማ ግርማ እና አትሌት መዝገቡ ስሜ ደግሞ በቅደም ተከተል 2ኛ እና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ…
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብሮች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬም ቀጥሎ ሲካሄድ አርሰናል ከበርንማውዝ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ ቀን 8 ሰዓት ከ30 በምሳ ሰዓት የጨዋታ መርሐ ግብር አስቶንቪላ ከፉልሃም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ቀን 11 ሰዓት ላይ ደግሞ ኤቨርተን ከኢፕስዊች ታውን እንዲሁም ከፕሪሚየር…
ባሕርዳር ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባሕርዳር ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 2 ለ 0 አሸንፏል።
የጣና ሞገዶቹን የማሸነፊያ ግቦች ግርማ ዲሳሳ እና ቸርነት ጉግሳ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ ቀጥሎ በተካሄደው የሊጉ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና መቻል 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት…