ስፓርት
አትሌት ሲምቦ ዓለማየሁ እና ሎሚ ሙለታ ለፍጻሜ አለፉ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች መሰናክል ማጣሪያ ውድድር አትሌት ሲምቦ ዓለማየሁ እና ሎሚ ሙለታ ለፍጻሜ ደርሰዋል፡፡
አትሌት ሎሚ ከምድቧ 5ኛ እንዲሁም ሲምቦ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ነው ለፍጻሜው ያለፉት፡፡
የፍጻሜው ውድድር ሐምሌ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት 4 ሠዓት ከ10 ላይ እንደሚካሄድ የወጣው መርሐ-ግብር ያመላክታል፡፡
Read More...
ኢትዮጵያ የምትሳተፍባቸው የማጣሪያ ውድድሮች ዛሬ ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2024 ፓሪስ ኦሊምፒክ በተለያዩ ርቀቶች ኢትዮጵያ የምትሳተፍባቸው ሦስት የማጣሪያ ውድድሮች ይካሄዳሉ፡፡
በዚህም መሠረት ቀን 5 ሠዓት ከ5 ላይ በሚካሄደው 3 ሺህ ሜትር የሴቶች መሰናክል ማጣሪያ ውድድር ÷ አትሌት ሎሚ ሙለታ እና ሲምቦ ዓለማየሁ ይሳተፋሉ፡፡
እንዲሁም ምሽት 3 ሠዓት ከ35 ላይ በሚካሄደው 800 ሜትር…
የኢትዮጵያ ሴቶች እግር ኳስ ሽልማት ተከናወነ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2016 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ውድድር የእውቅና ሥነ-ስርዓት ተከናውኗል፡፡
በመርሐ-ግብሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት እና የካፍ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ባሕሩ ጥላሁን፣ የሥራ…
በ800 ሜትር ሴቶች ማጣሪያ አትሌት ፅጌ ዱጉማና ወርቅነሽ መሰለ ወደ ግማሽ ፍፃሜ አለፉ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ ኦሊምፒክ በ800 ሜትር ሴቶች ማጣሪያ አትሌት ፅጌ ዱጉማና ወርቅነሽ መሰለ ወደ ግማሽ ፍፃሜ አልፈዋል፡፡
ምሽት 2 ሠዓት ከ45 ላይ 800 ሜትር የሴቶች ማጣሪያ ውድድር ተካሂዷል፡፡
በዚህም በምድብ ሁለት አትሌት ወርቅነሽ መሰለ 1፡58.07 እንዲሁም በምድብ ሶስት አትሌት ፅጌ…
በ5 ሺህ ሜትር ሴቶች ማጣሪያ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ፣ እጅጋየሁ ታዬና መዲና ኢሳ ለፍፃሜ አለፉ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ ኦሎምፒክ 5 ሺህ ሜትር ሴቶች ማጣሪያ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ፣ እጅጋየሁ ታዬና መዲና ኢሳ ለፍፃሜ አልፈዋል፡፡
ምሽት 1 ሠዓት ከ10 ላይ በ5 ሺህ ሜትር ሴቶች ማጣሪያ ተካሂዷል፡፡
በዚህም በምድብ አንድ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ 14፡57፡84፣ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ 14፡57፡97 በሆነ ሰዓት በመግባት ለፍፃሜው ማለፋቸውን…
በ1 ሺህ 500 የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ኤርሚያስ ግርማና ሳሙኤል ተፈራ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፉ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ33ኛው ኦሊምፒክ ጨዋታዎች የ1 ሺህ 500 ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ኤርሚያስ ግርማ እና ሳሙኤል ተፈራ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አልፈዋል፡፡
በምድብ ሁለት የተወዳደረው ኤርሚያስ 3 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ ከ21 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት ነው ውድድሩን በቀዳሚነት በማጠናቀቅ ለግማሽ ፍፃሜ የበቃው፡፡
በተመሳሳይ በምድብ ሶስት…
ኢትዮጵያ የምትጠበቅበት የ10 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ፍጻሜ ዛሬ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ የምትጠበቅበት የ10 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ፍጻሜ ዛሬ ይካሄዳል፡፡
የ10 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ ፍጻሜ ከምሽቱ 4 ሠዓት ከ 20 ላይ እንደሚካሄድ የወጣው መርሐ-ግብር ያመላክታል፡፡
የማሸነፍ ቅድመ ግምት የተሰጣት ኢትዮጵያም በፍጻሜው በአትሌት ሰለሞን ባረጋ፣ ዮሚፍ ቀጄልቻ እና…