Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ 26ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሠዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል። የሊጉ ጨዋታ አመሻሽ 12 ሠዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ አርባ ምንጭ ከተማ እና ስሑል ሽረ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
Read More...

ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች፤ ቢንያም ፍቅሩ (2) እና አብዱ ሳሚዮ ሲያስቆጥሩ፤ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን ከሽንፈት ያልታደገች ብቸኛ ግብ ደግሞ ቡልቻ ሹራ ከመረብ አሳርፏል፡፡…

ማንቼስተር ሲቲ ኤቨርተንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ኤቨርተንን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የማንቼስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኦ-ሬልይ እና ኮቫቺች ማስቆጠር ችለዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ በ58 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፤ ኤቨርተን በ38 ነጥብ 13ኛ ደረጃ ላይ…

ሀድያ ሆሳዕና ወላይታ ድቻን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሀድያ ሆሳዕና ወላይታ ድቻን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የሀድያ ሆሳዕናን የማሸነፊያ ግቦች ብሩክ በየነ፣ በየነ ባንጃ እና ደስታ ዋሚሾ ሲያስቆጥሩ፤ የወላይታ ድቻን ብቸኛ ጎል ዘላለም አባተ ከመረብ አሳርፏል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም ሀድያ ሆሳዕና ወደ ድል ሲመለስ፤…

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 5 ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብር አምስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ። ዛሬ ከሚደረጉ ጨዋታዎች መካከል ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ አስቶንቪላ በሜዳው ቪላ ፓርክ ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል። በ54 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው አስቶንቪላ በፒኤስጂ በድምር ውጤት ከአውሮፓ…

ነገሌ አርሲ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አደገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ለ እየተሳተፈ የሚገኘው ነገሌ አርሲ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል። ዛሬ የምድብ 21ኛ ጨዋታውን ያደረገው ነገሌ አርሲ ስልጤ ወራቤን 3 ለ 0 አሸንፏል። ውጤቱን ተከትሎም ክለቡ አንድ ጨዋታ እየቀረው በ46 ነጥብ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል፡፡

የፀረ አበረታች ቅመሞች ምርመራን ለማሳደግ እየሠራሁ ነው- ፌዴሬሽኑ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በፀረ አበረታች ቅመሞች ላይ አሠራሩን ለማዘመን እና ምርመራዎችን ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን አስታወቀ፡፡ ለዚህም ከዓለም አትሌቲክስ ጋር በመተባበር አትሌቶች ባሉበት ሆነው እንዲሁም በክልሎች እና ከተማ አሥተዳደሮች ኮሚቴ በማቋቋም ለአትሌቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑ…