Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ቅዱስ ጊዮርጊስ አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ አዳማ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ፍፁም ጥላሁን በሁለተኛው አጋማሽ አስቆጥሯል፡፡ ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ35 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ አዳማ ከተማ በበኩሉ በ33 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ አዳማ ከተማ በሊጉ ተከታታይ ስድስተኛ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
Read More...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 29ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ በጉባኤው መክፈቻ ላይ አዲሱ የፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ በአንድ ዓመት ውስጥ በርካታ ተግባራት ማከናወኑን አንስተዋል፡፡ የአትሌቲክሱን ዘርፍ ለማሳደግ ፌዴሬሽኑ ከመንግስት ጋር በመተባበር…

ማንቼስተር ሲቲ አርሰናልን በማሸነፍ ነጥቡን አጠበበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ተጠባቂ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ አርሰናልን 2 ለ 1 አሸንፏል። በሜዳው ኢትሃድ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ የሊጉን መሪ አርሰናልን ያስተናገደው ማንቼስተር ሲቲ ቼሪኪ እና ሃላንድ ባስቆጠሯቸው ግቦች ነጥቡን ወደ ሶስት ለማጥበብ ያስቻለውን ድል አስመዝግቧል።…

ሊቨርፑል እና አስቶን ቪላ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ 

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ 33ኛ ሳምንት ጨዋታ ሊቨርፑል እና አስቶን ቪላ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡ በመርሲሳይድ ደርቢ ከኤቨርተን ጋር ጨዋታውን ያደረገው ሊቨርፑል 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ሞሀመድ ሳላህ እና ቨርጂል ቫንዳይክ ለሊቨርፑል እንዲሁም ቤቶ ለኤቨርተን ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡ በተመሳሳይ ጨዋታ በቪላ ፓርክ…

ማንቼስተር ሲቲ ከአርሰናል – የሳምንቱ ተጠባቂ ፍልሚያ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ የሊጉን መሪ አርሰናልን ያስተናግዳል፡፡ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡትን ቡድኖች የሚያገናኘው ጨዋታ የሳምንቱ ተጠባቂ መርሐ ግብር ነው፡፡ ማንቼስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል…

በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር 10 ሺህ ሜትር ሩጫ አትሌት ፋንታዬ አዳነ እና ይስማው ድሉ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር 10 ሺህ ሜትር ሩጫ አትሌት ፋንታዬ አዳነ እና ይስማው ድሉ አሸንፈዋል። የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የአትሌቲክስ ውድድር ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም እየተካሄደ ነው። በዚህም በ10 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር በሴቶች አትሌት ፋንታዬ አዳነ በቀዳሚነት አጠናቅቃለች።…

ቼልሲ ከማንቼስተር ዩናይትድ …

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ከማንቼስተር ዩናይትድ የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡ ሁለቱም ቡድኖች የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን ለማግኘት የሚያደርጉትን ጉዞ አጠናክረው ለመቀጠል የሚያደርጉት ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡ በሊጉ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ ጨዋታዎች የተሸነፈው ቼልሲ ወደ…