ስፓርት
ሀዲያ ሆሳዕና አዳማ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 10ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሀዲያ ሆሳዕና አዳማ ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸነፈ።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕና ኢዮብ አለማየሁ እና በረከት ወ/ዮሐንስ ባስቆጠሯቸው ሁለት ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።
በተመሳሳይ ቀን 10 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው የሊጎ 10ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ስሑል ሽረ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተለያይተዋል።
Read More...
ኢትዮጵያ ቡና አርባ ምንጭ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በ10ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና አርባ ምንጭ ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ፡፡
10 ሠዓት ላይ በተከናወነው ጨዋታ ለኢትዮጵያ ቡና የማሸነፊያ ግቦቹን ከዕረፍት መልስ ዲቫይን ዋቹኩዋ እና ኦካይ ጁል አስቆጥረዋል፡፡
በተመሳሳይ ምሽት 1 ሠዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ባሕር ዳር ከተማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 3…
አርሰናል ከማንቼስተር ዩናይትድ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ14ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብሮች ሲደረጉ ምሽት 5 ሠዓት ከ15 ላይ አርሰናል በኤምሬትስ ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ በጉጉት ይጠበቃል፡፡
በቡድኖቹ መካካል በተለይም ከፈረንጆቹ 1996 እስከ 2004 የነበረው ብርቱ ፉክክር÷ በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ቀደም ሲልም ሆነ ከዚያ በኋላ…
በአርባምንጭ ከተማ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 25፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ የ5 ኪሎ ሜትር ታላቅ ሩጫ በአርባምንጭ ከተማ ተካሂዷል፡፡
የጎዳና ላይ ሩጫው በህዝብ ተሳትፎና በክልሉ መንግሥት ድጋፍ እየተገነባ ለሚገኘው የአርባ ምንጭ ዓለም ዓቀፍ ስታዲየም ግንባታ ገቢ ለማሰባሰብ እንዲሁም በከተማው የሚከበረውን የብሔር፣…
በጊኒ የእግር ኳስ ዳኛ ውሳኔን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት የ56 ሰዎች ሕይወት አለፈ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 23፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በጊኒ የእግር ኳስ ዳኝነት ላይ የተላለፈን ውሳኔ ተከትሎ በተፈጠረ ግጭትና መረጋገጥ የ56 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡
በጊኒ ንዜርኮሬ ከተማ በተደረገ የእግር ኳስ ጨዋታ ላይ ላቤ የተሰኘ የእግር ኳስ ክለብ ላይ የተላለፈ የዳኝነት ውሳኔን ተከትሎ ደጋፊዎች ድንጋይ መወርወር መጀመራቸው ተመላክቷል፡፡
ግጭቱን ለመቆጣጠርም…
የመቻል ስፖርተኞች በስፖርቱ ዘርፍ የኢትዮጵያ አደራ አለባቸው – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 23፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመቻል ስፖርተኞች በስፖርቱ ዘርፍ ከተቋም ባለፈ የኢትዮጵያ አደራ አለባቸው ሲሉ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ፡፡
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በናይጀሪያ አቡጃ በመላው አፍሪካ የጦር ሃይሎች ስፖርት ፌስቲቫል ተካፋይ ለነበረው የመቻል አትሌቲክስ ቡድን አቀባበል አድርገዋል።…
አትሌት ታምራት ቶላ እና አትሌት ሲምቦ አለማየሁ የአመቱ ምርጥ አትሌቶች ተባሉ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ታምራት ቶላ ከስታዲየም ውጭ የዓመቱ ምርጥ የጎዳና ላይ ውድድር አትሌት ሽልማትን አሸንፏል፡፡
አትሌት ታምራት ቶላ በፓሪስ ኦሎምፒከ አዲስ ክብረ ወሰን በማሻሻል በማሸነፍ ለሀገሩ ብቸኛውን ወርቅ ሜዳሊያ ማስገኘቱ ይታወሳል።
ሌላኛዋ አትሌት ሲምቦ አለማየሁ ደግሞ የዓመቱ ምርጥ ታዳጊ አትሌት ሽልማትን ማሸነፏን የዓለም…