Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ፒኤስጂ ከአርሰናል ለሙኒኩ ፍጻሜ….

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ በግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ ፒኤስጂ በሜዳው ፓርክ ደ ፕሪንስ ዛሬ ምሸት 4 ሰዓት ላይ አርሰናልን ያስተናግዳል። የዛሬ ምሽት የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚ ቡድኖች በታሪካቸው አንድም ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን አሳክተው አያውቁም። ሁለቱ ቡድኖች ኤሚሬትስ ላይ ባደረጉት የመጀመሪያ ዙር የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ በኦስማን ዴምቤሌ ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል። የፈረንሳይ ሊግ ኧ ዋንጫን አስቀድሞ…
Read More...

ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ ኤሌክትሪክን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ብቸኛ ግብ አማኑኤል ኤርቦ ከመረብ አሳርፏል፡፡ የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ቀን 9 ሰዓት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወልዋሎ ዓዲግራት…

አዳማ ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ28ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አዳማ ከተማ ከመቐለ 70 እንደርታ ያደረጉት ጨዋታ ያለምንም ጎል አቻ ተጠናቅቋል፡፡ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም እየተካሄደ የሚገኘው የ28ኛ ሣምንት መርሐ ግብር ሲቀጥል፤ 12 ሠዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከሀድያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

አሌክሳንደር አርኖልድ ከልጅነት ክለቡ ጋር እንደሚለያይ አረጋግጧል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከልጅነት ክለቡ ሊቨርፑል ለመልቀቅ መወሰኑን አስታውቋል፡፡ አሌክሳንደር አርኖልድ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው መረጃ፤ ራሱን በአዲስ ክለብ እና በተለየ ቦታ ለመፈተሽ በመፈለጉ ከሊቨርፑል ለመልቀቅ መወሰኑን አስታውቋል፡፡ ወደ አዲስ ክለብ መሄዱም ያለውን ሙሉ አቅም…

ቼልሲ ከሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ በስታምፎርድ ብሪጅ ሊቨርፑልን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጠበቃል። ለቀጣይ ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ እየተፎካከሩ የሚገኙት ሰማያዊዎቹ ምሽት 12:30 የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ካረጋገጠው ሊቨርፑል ጋር ይጫወታሉ። በጨዋታው መጀመሪያ…

አርሰናል በበርንማውዝ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በሜዳው ኤሚሬትስ ስታዲየም በርንማውዝን ያስተናገደው አርሰናል 2 ለ 1 ተሸንፏል፡፡ የበርንማውዝን የማሸነፊያ ግቦች ዲያን ሁጅሰንና ኢቫኒልሰን ሲያስቆጥሩ አርሰናልን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ዲክላን ራይስ ከመረብ አሳርፏል፡፡ ቀደም ብለው በተደረጉ…

ኢትዮጵያ መድን አርባ ምንጭ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን አርባ ምንጭ ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ቀን 9 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አለን ካይዋ እና አቡበከር ሳኒ የመድንን የማሸነፊያ ግቦች አስቆጥረዋል፡፡ የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሃዋሳ…