ስፓርት
ባህር ዳር ከተማ 3ኛ ደረጃን ይዞ የውድድር ዓመቱን አጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የባህርዳር ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ሙጂብ ቃሲም፣ በረከት ጥጋቡ እና ይሄነው የማታው አስቆጥረዋል፡፡
ባህር ዳር ከተማ 54 ነጥብ በመሰብሰብ 3ኛ ደረጃን በመያዝ የውድድር ዓመቱን አጠናቅቋል፡፡
አስቀድሞ ከሊጉ የወረደው ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ካደረጋቸው 34 ጨዋታዎች 19 ነጥብ በመሰብሰብ 18ኛ ደረጃን በመያዝ የውድድር ዓመቱን ቋጭቷል፡፡
የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት…
Read More...
አዳም ላላና ራሱን ከእግር ኳስ አገለለ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የሊቨርፑል የቀድሞ ተጫዋች አዳም ላላና ራሱን ከእግር ኳስ አግልሏል።
የመሐል ሜዳ ተጫዋቹ አዳም ላላና በ37ዓመቱ ጫማ መስቀሉን በዛሬው ዕለት አረጋግጧል፡፡
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቆይታው በ305 ጨዋታዎች የተሳተፈ ሲሆን÷ ለእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ደግሞ 34 ጨዋታዎችን አድርጓል፡፡
አዳም ላላና…
ተጠባቂው የ90 ደቂቃ ፍልሚያ…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ መድንን ሻምፒዮን በማድረግ ከሊጉ ከሚሰናበቱ አራት ክለቦች መካከል 3ቱን ከወዲሁ ወደ ከፍተኛ ሊግ ሸኝቶ የውድድር አመቱን ሊቋጭ ሦስት ጨዋታዎች ብቻ ቀርተውታል፡፡
አዳማ ከተማ፣ ስሑል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን ተከትሎ ከፕሪሚየር ሊጉ የሚወርደውን ክለብ የሚወስነው የ90 ደቂቃ…
አዳማ ከተማ ከፕሪሚየር ሊጉ ወረደ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አዳማ ከተማ በሀዋሳ ከተማ ተሸንፎ ከፕሪሚየር ሊጉ ወርዷል፡፡
ዛሬ 9፡00 ላይ የተደረገው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ በሀዋሳ ከተማ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
የሀዋሳ ከተማን ግቦች አቤኔዘር ዮሐንስ እና በረከት ሳሙኤል ሲያስቆጥሩ፥ አዳማ ከተማን ከሽንፈት…
ወላይታ ድቻ ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 በማሸነፍ በውድድር ዓመቱ የመጨረሻ ጨዋታውን በድል ቋጭቷል፡፡
የወላይታ ድቻን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቴዎድሮስ ኃይለማርያም ሲያስቆጥር፥ ድሉን ተከትሎ ክለቡ 48 ነጥብ በመያዝ መርሐ ግብሩን አጠናቅቋል፡፡
43 ነጥብ በመያዝ የውድድር…
ኢትዮጵያ ቡና እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውድድር ዓመቱን በአቻ ውጤት አጠናቀቁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 2 ለ 2 አቻ ተለያዩ፡፡
የኢትዮጵያ ቡናን ግቦች እስራኤል ሸጎሌ እና ዮሀንስ ኪዳኔ ሲያስቆጥሩ፥ ወልደአማኑኤል ጌቱ እና ኪቲካ ጅማ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኳስና መረብን አገናኝተዋል፡፡
ሁለቱ ክለቦች በሊጉ የመጨረሻ ጨዋታ…
ሊቨርፑል ፍሎሪያን ቪርትስን ከባየር ሊቨርኩሰን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊቨርፑል ጀርመናዊውን የአጥቂ አማካይ ፍሎሪያን ቪርትስ የክለቡ የዝውውር ክብረ ወሰን በሆነ ዋጋ ከባየር ሊቨርኩሰን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።
ሊቨርፑል ለተጫዋቹ ዝውውር 100 ሚሊየን ፓውንድ እና ተጨማሪ 16 ሚሊየን ፓውንድ የሚከፍል ሲሆን፥ ለአምስት አመት በአንፊልድ የሚያቆየውን ውል ፈርሟል።
ፍሎሪያን ቪርትስ…