Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ማድረግ ያስቻለ የዲፕሎማሲ ሥራ ተሰርቷል – ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ማድረግ ያስቻለ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ሥራ ተሰርቷል አሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ። ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 34ኛ መደበኛ…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከስሎቬንያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከስሎቬንያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሻ ፒሪክ ሙሳር ጋር ተወያይተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መረጃ÷ ዛሬ ጠዋት ኢትዮጵያን እየጎበኙ ያሉትንና በስሎቬንያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት…

5ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ ሰኔ 7 ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 5ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር የፊታችን ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም ይጀመራል፡፡ በውድድሩ የምዕራፍ 17፣ 18 እና 19 አሸናፊዎች እንዲሁም ምርጥ አራት ተሰናባቾች ዳግም ተመልሰው በአጠቃላይ 16 ተወዳዳሪዎች ይሳተፋሉ፡፡…

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 47ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች እንደሚከተለው ቀርቧል፡- 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የ2018 በጀት ዓመት…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከ231 ሺህ በላይ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እየተሰራጨ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለ2017/18 ምርት ዘመን 231 ሺህ 340 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እና 5 ሺህ 292 ኩንታል ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ ነው፡፡ በክልሉ ግብርና ቢሮ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ፈቃዱ ወዬሳ ለፋና ዲጂታል…

በአፋር ክልል የአብዬ ሃይቅን የቱሪስት መዳረሻነት ለማስፋት እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፋር ክልል አፋምቦ ወረዳ የአዋሽ ወንዝ መዳረሻ ላይ የሚገኘውን የአብዬ ሃይቅ የቱሪስት መዳረሻነት ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ መሐመድ አሊ ቢኢዶ ÷በ2017 በጀት ዓመት በአፋር ክልል ያለውን…

አዳማ ከተማ ባሕር ዳር ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አዳማ ከተማ ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ የአዳማ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ቢንያም አይተን እና ሙሴ ኪሮስ በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡ አዳማ ከተማ ተከታታይ…

ሁዋጂያን በገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በሶላር ምርትና ኤክስፖርት ዘርፍ ሊሰማራ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቻይናው ሁዋጂያን ግሩፕ በገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ለመሰማራት የ100 ሚሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱን የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሞቱማ ተመስገን እና የሁዋጂያን ግሩፕ ሥራ አስፈጻሚ…

የገጠሩን ማሕበረሰብ አኗኗር ለማሻሻል የገጠር ኮሪደር በሁሉም አካባቢዎች እየተስፋፋ ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የገጠሩን ማሕበረሰብ አኗኗር ለማሻሻል የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት በሁሉም አካባቢዎች እየተስፋፋ ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ዛሬ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ…

በኦሮሚያ ክልል የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም 61 በመቶ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል ወደ ውጪ ከተላኩ ምርቶች 837 ሚሊየን ዶላር ገቢ ተገኝቷል አለ የክልሉ የኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ አሕመድ ኢድሪስ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ በክልሉ ያለውን የኢንቨስትመንት አገልግሎት አሰጣጥ ምቹና…