Fana: At a Speed of Life!

የቀድሞው የማንቼስተር ሲቲ ተጨዋች ሚካይል ኬቬላቪሊ የጆርጂያ ፕሬዚዳታዊ ምርጫን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዙ ማንቼስተር ሲቲ እና ሌሎች ክለቦች በእግርኳስ ተጫዋችነት ያሳለፉት ሚካይል ኬቬላቪሊ የጆርጂያ ፕሬዚዳታዊ ምርጫን ማሸነፋቸው ተገለፀ፡፡ የ53 አመቱ ጎልማሳ ከ300 የሀገሪቱ ፓርላሜንታዊ የምርጫ ድምፅ 224 በማሸነፍ ነው የተመረጡት፡፡…

በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ42 ሚሊየን በላይ መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ትግበራ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን ቁጥር ከ42 ሚሊየን በላይ ለማድረስ ማስቻሉን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን አለማየሁ (ዶ/ር)÷ ባለፉት አራት አመታት…

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካቢኔ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለማሻሻል በወጣ ደንብ ዙሪያ ተወያይቶ አስተያየትና ግብዓቶችን በማከል ወደ…

የአንካራው ስምምነት ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሰላም ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው – አቶ ሙስጠፌ መሃመድ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአንካራው ስምምነት ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን የሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ገለፁ። በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተደረሰውን የአንካራ ስምምነት ተከትሎ የሶማሌ ክልል ከፍተኛ…

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ለልማት ጉልህ ፋይዳ ያላቸው አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ስብሰባ ለከተማዋ ልማት ጉልህ ፋይዳ ያላቸው አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ አፅድቋል፡፡ በዚህም:- 1ኛ. የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ብክለት መከላከል ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ…

የአንካራው ስምምነት እና የቀጣናውን ሰላም የማይፈልጉ ኃይሎች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መንግስት መካከል የተደረሰው የአንካራ ስምምነት የቀጣናውን ሰላም የማይፈልጉ ኃይሎችን ዕኩይ ተልዕኮ ማክሸፉን ምሁራን ገለፁ፡፡ የሀገራቱ መሪዎች አንዳቸው የሌላኛውን ሉዓላዊነት፣ ነጻነት እና የግዛት አንድነት እንዲሁም…

የምስራቅ አፍሪካ የህጻናት ፖሊሲ ማዕቀፍ ጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የህጻናት ጉዳይ የሚመለከታቸው ሚኒስትሮች የቀጣናውን የህጻናት ፖሊሲ ማዕቀፍ አጸደቁ፡፡ የፖሊሲ ማዕቀፉ በቀጣናው የሚኖሩ ህጻናት የሚያጋጥማቸውን ችግር በመፍታት ደህንነታቸውን…

የሰላም ሚኒስቴር እና ዩኒሴፍ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰላም ሚኒስቴር እና የተባበሩት መንግስታት የሕጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በግጭት መከላከል እና በሰላም ግንባታ ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል። የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ የተባበሩት መንግስታት የሕጻናት መርጃ…

ሩሲያ በዩክሬን ኢነርጂ መሰረተ ልማቶች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ፈጸመች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሩሲያ በዩክሬን ኢነርጂ መሰረተ ልማቶች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት መፈጸሟን አስታወቀች፡፡ ጥቃቱ ከቀናት በፊት ዩክሬን በሩሲያ ታጋኖርግ ግዛት ለፈጸመችው የሚሳኤል ጥቃት አጸፋ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር…

የአንካራው ስምምነት በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል ጠንካራ ትብብር እንዲኖር ያስችላል – ፕሬዚዳንት ታዬ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአንካራው ስምምነት በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል ጠንካራ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትስስር እንዲኖር የሚያስችል ነው ሲሉ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለፁ፡፡ ፕሬዚዳንቱ በኤክስ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ስምምነቱ ኢትዮጵያና…