Fana: At a Speed of Life!

የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በአጋሮ ከተማ ያስገነባው የዳቦ እና ዱቄት ፋብሪካ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በአጋሮ ከተማ ያስገነባው የዳቦ እና ዱቄት ፋብሪካ ተመረቀ፡፡ ፋብሪካው በቀን 300 ሺህ ዳቦና 42 ቶን ዱቄት የማምረት አቅም አለው። ፋብሪካውን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ሰባት ወራት የፈጀ ሲሆን÷ የግንባታ ሥራውም…

በምሥራቅ ሐረርጌ በትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ግራዋ ወረዳ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ዲቪዥን ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ቶሎሳ ጎሹ እንደገለፁት÷ ትናንት ከምሽቱ 4፡45 አካባቢ…

በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ መንግሥት እያደረገ ያለውን ጥረት የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በተለያዩ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ መንግስት እያደረገ ያለውን ጥረት የሚደግፍ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡ በተሁለደሬ፣ ሀይቅ፣ ቃሉ፣ ከለላ፣ ወረባቦ፣ ተንታ፣ ሀርቡ፣ በወልዲያ፣…

ለዘላቂ ሰላም አሸባሪው ህወሓት ትጥቅ ይፍታ፤ የሽብር ቡድኑን እስትንፋስ ለማራዘም የሚሠሩ እጆች ይሰብሰቡ- የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለዘላቂ ሰላም አሸባሪው ህወሓት ትጥቅ ይፍታ፤ የሽብር ቡድኑን እስትንፋስ ለማራዘም የሚሠሩ እጆች ይሰብሰቡ ሲሉ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ጠየቁ፡፡ በኢትዮጵያ ላይ የሚደረግን ያልትገባ ጫና የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ በደብረብርሃን ከተማ…

በጎንደር የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚያወግዝ ሕዝባዊ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማ የውጭ ጣልቃ ገብነትን እና አሸባሪው ህወሓትን የሚያወግዝ ሕዝባዊ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡ ሰልፉ የተካሄደው÷ "ለኢትዮጵያ እቆማለሁ፤ ድምፄን አሰማለሁ" በሚል መሪ ሐሳብ ነው፡፡ ሕዝባዊ ሰልፉ ጀግኖች አርበኞች፣ የሐይማኖት አባቶች፣…

አንዳንድ ምዕራባውያን በውስጥ ጉዳያችን ጣልቃ በመግባታቸው ለሰላማችን እንቅፋት ሆነዋል- የደሴ ከተማ ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አንዳንድ የምዕራባውያን ሀገራት በውስጥ ጉዳያችን ጣልቃ በመግባታቸው ለሰላማችን እንቅፋት ሆነዋል ሲሉ የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ በደሴ ከተማ አሸባሪው ህወሓትን እና የምዕራባውያንን ጣልቃ ገብነት የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡ የከተማዋ…

“በሰብዓዊ እርዳታ ስም የሚደረግ ጣልቃ ገብነት ይቁም” – የባሕርዳር ከተማ ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የባሕዳር ከተማ ነዋሪዎች በሰብዓዊ እርዳታ ስም የሚደረግ ጣልቃ ገብነት እንዲቆም እና በውክልና ጦርነት መጠቃት እንዲያበቃ ጠየቁ፡፡ ባሕርዳር ከተማ የምዕራባውያንን ያልተገባ ጣልቃገብነት እና አሸባሪው ህወሓትን የሚያወግዝ ሰልፍ…

በሐዋሳ የብስክሌተኞችና የእግረኞች ጉዞ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “በትራፊክ አደጋ የሚደርሰውን አደጋ ለመቀነስ እኔም ድርሻ አለኝ” በሚል መሪ ሐሳብ በሐዋሳ ከተማ ሀገር አቀፍ የብስክሌተኞችና የእግረኞች ጉዞ ተካሂዷል፡፡ በጉዞው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ እና የሲዳማ ክልል…

በኮምቦልቻ ከተማ የውጭ ጣልቃ ገብነትን የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኮምቦልቻ ከተማ አሸባሪው ህወሓትን እና የምዕራባውያንን ጣልቃ ገብነት የሚያወግዝ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡ ሕዝባዊ ሰልፉ የተካሄደው÷ “ለኢትዮጵያ እቆማለሁ፤ ድምጼን አሰማለሁ” በሚል መሪ ሐሳብ ነው፡፡ የከተማዋ ነዋሪዎች “በውክልና…

ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የአቪዬተርስ አፍሪካ ሽልማት ተሸለሙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪ አርአያ ለሆኑ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የሚሰጠውን የአቪዬተርስ አፍሪካ ሽልማት ፕሮግራም በለውጥ ፈጣሪዎች ምድብ ተሸለሙ፡፡ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ በተካሄደው 4ኛው…