Browsing Category
ቢዝነስ
ባለፉት ስድስት ወራት ከወጪ ምርት የተገኘው 5 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር በሙሉ ዓመት ተገኝቶ አያውቅም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፉት ስድስት ወራት ከወጪ ምርት የተገኘው 5 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ከዚህ ቀደም በሙሉ ዓመት እንኳን ተገኝቶ አያውቅም አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ…
ብሔራዊ ባንክ ያካሄደው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት ያካሄደውን የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ አድርጓል።
ለጨረታ 70 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር መቅረቡንና በሒደቱ 19 ባንኮች መሳተፋቸውን ጠቅሶ÷ 8 ባንኮች በጨረታው ማሸነፋቸውን ገልጿል።
በምንዛሪ ጨረታው…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-
👉 ለውጡ ከመጣ ጀምሮ ኢትዮጵያ አንድም ዶላር በኮሜርሻል ብድር አልወሰደችም ይህም ከፍተኛ ምስጋና የሚገባው ጠንካራ የፖሊሲ አቅጣጫ ነው።
👉 ያበደሩን ወዳጆቻችን ምንም እንኳን ብድሩ አራጣ ቢሆንም ተገቢ አይደለም እና ወደ ትክክለኛው የብድር ሥርዓት እንዲገባ የማድረግ ስራዎች ማከናወን ተችሏል።…
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 10 ነጥብ 7 ሚሊየን ሰዎችን አጓጉዟል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ስድስት ወራት 10 ነጥብ 7 ሚሊየን ሰዎችን አጓጉዟል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፥…
የኢትዮጵያ መድን ድርጅት 13 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ
አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት 13 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ገቢ አግኝቷል።
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቤል ታደሰ እንዳሉት ÷ በግማሽ ዓመቱ የተገኘው ገቢ ከባለፈው በጀት ዓመት በዓመቱ ከተገኘው የበለጠ…
የሕብረት ስራ ማህበራት ሚና ገበያን ለማረጋጋትና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ…
አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሕብረት ስራ ማህበራት ገበያን በማረጋጋት እና የኑሮ ውድነትን ከመቀነስ አንጻር ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ አሉ የኢትዮጵያ ሕብረት ሥራ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር አቶ ጌትነት ታደሰ።
“ሕብረት ሥራ ከምርት እስከ ግብይት፤ ከአምራች እስከ ሸማች" በሚል መሪ…
በግማሽ ዓመቱ 999 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተገኝቷል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ጥር 23 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት 999 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተገኝቷል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡
አይሻ-2 የንፋስ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፣ የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ…
የቁም እንስሳት ንግድ ሥርዓትን በማዘመን የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ…
አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የቁም እንስሳት ንግድ ሥርዓትን በማዘመን የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው አሉ።
ሚኒስትሩ በደቡብ ኦሞ ዞን በናፀማይ ወረዳ ቀይ አፈር ከተማ ‘የቀይ አፈር 2ኛ ደረጃ የቁም…
የቡና ሀብትን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ…
አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቡና ሀብትን የቱሪዝም መዳረሻ እንዲሆን ለማድረግ በትኩረት መስራት ይገባል አለ የቱሪዝም ሚኒስቴር።
ሀገር አቀፍ የቡና ቱሪዝም ሴሚናር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በቱሪዝም ሚኒስቴር የቱሪዝም…
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ የመለያ (ብራንድ) ለውጥ አደረገ
አዲስ አበባ፣ 22 ጥር፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አንበሳ ባንክ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ለማቀላጠፍ የሚያስችል የመለያና የስያሜ ለውጥ አድርጌያለሁ አለ።
ባንኩ የስያሜና የሎጎ ለውጥ ያደረገበትን አዲስ ብራንድ ይፋ አድርጓል።
ከዚህ ቀደም "አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ"…