Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ የካፒታል ዕቃዎች የፋይናንስ ማህበር ተመሰረተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የካፒታል ዕቃዎች የፋይናንስ ማህበር በይፋ ተመስርቷል። በምስረታው ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት፣ የገንዘብ ሚኒስቴርና ሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማት ሃላፊዎች ተገኝተዋል። የማህበሩ…

በአፋር ክልል ከ3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፋር ክልል ባለፉት 10 ወራት ከ3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታውቋል። የቢሮው ሃላፊ አቶ አወል አብዱ እንደተናገሩት÷ በክልሉ የገቢ አማራጮችን በማስፋት የሚሰበሰበውን ገቢ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ…

በክልሉ ለግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የእውቅና እና የሽልማት መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የእውቅና እና የሽልማት መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው። በመርሐ ግብሩ የክልሉ ም/ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)፣ የገቢዎች ሚኒስትር ዴዔታ ተስፋዬ…

አዋሬ ያላሰለሰ ጥረት የነዋሪዎችን የኑሮ ዘይቤና ተስፋ ከፍ ሊያደርግ እንደሚችል ማሳያ ምልክት ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)አዋሬ ያላሰለሰ ጥረት የነዋሪዎችን የኑሮ ዘይቤና ተስፋ ከፍ ሊያደርግ እንደሚችል ማሳያ ምልክት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፤ "ዛሬ በአዋሬ አካባቢ ከስድስት…

የሳዑዲ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን የኢንቨስትመንትና ንግድ ተሳትፎ እንዲያጠናክሩ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ከሳዑዲ አረቢያ የንግድ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሀሰን ሙጂብ ኦል ህዋይዚ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም፤ የሳዑዲ አረቢያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ እያደረጉት ያለውን የኢንቨስትመንት እና ንግድ ተሳትፎ…

ኢትዮጵያ ቀጣዩን የ “አይ ዲ 4 አፍሪካ” ጉባዔን እንድታስተናግድ ተመረጠች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በ2025 የሚካሄደውን የ “አይ ዲ 4 አፍሪካ” ጠቅላላ ጉባዔ አዘጋጅ ሀገር ሆና ተመረጠች፡፡ የ “አይ ዲ 4 አፍሪካ” ሊቀ መንበር ጆሴፍ ጄ ሃቲክ (ዶ/ር) በደቡብ አፍሪካ-ኬፕታወን እየተካሄደ በሚገኘው የድርጅቱ የ2024 ጉባዔ ላይ…

አሽከርካሪዎችና ረዳቶችን እያስፈራሩ መኪኖችን ሲዘርፉ የነበሩ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አሽከርካሪዎችና ረዳቶችን በጦር መሳሪያ እያስፈራሩና ጫካ ውስጥ በገመድ እያሰሩ መኪኖችን ሲዘርፉ የነበሩ ግለሰቦች እስከ 19 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ተቀጡ። ለውንብድና ተግባር በቡድን በመደራጀት የሁለት አይሱዙና የአንድ ሲኖ ትራክ…

የጋምቤላ ክልል በማኅበራዊ ሚዲያ ሐሰተኛ መረጃ የሚያራግቡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል የሰላም ሁኔታ እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ አመራሮች እና በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች ተገቢ ያልሆኑ መረጃዎችን የሚያራግቡ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የክልሉ መንግሥት አሳሰበ፡፡ የጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት…

ማዳበሪያን በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ለማድረስ ርብርቡ እንዲጠናከር ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትራንስፖርት አፕሬተሮች የአፈር ማዳበሪያን በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሥራቸውን በትጋት እንዲቀጥሉ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ጠየቀ፡፡ ሚኒስቴሩ የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዝ ሥራ አፈፃፀምን አስመልክቶ ከትራንስፖርት…

በፓሪስ ኦሊምፒክ  ዳያስፖራዎች በውድድሩ ቦታ ተገኝተው አትሌቶችን እንዲያበረታቱ ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ ኦሊምፒክ ከ200 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራዎች በውድድር ስፍራ ተገኝተው አትሌቶችን እንዲያበረታቱ እየተሰራ መሆኑ ተመላከተ። በፓሪስ ኦሊምፒክ ውጤታማ ለመሆን የሚያስችል ጠንካራ ስራ እየተሰራ እንደሆነ የፓሪስ ኦሎምፒክ የብሔራዊ…