Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

ዓለምአቀፋዊ ዜና

ብሪክስ ራሱን የቻለ የፋይናንስ ሥርዓት ሊጀምር መሆኑ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ብሪክስ ራሱን የቻለ የፋይናንስ ሥርዓት ሊጀምር መሆኑን ሩሲያ አስታወቀች፡፡ በቻይና ቤጂንግ በተካሄደው 12ኛው የዓለም የሰላም ፎረም ላይ፥ ሩሲያ ከብሪክስ ሀገራት ጋር በብሔራዊ ምንዛሬ የምታደርገው የንግድ ልውውጥ መጠን በየጊዜው እያደገ መሆኑ…

ማሱድ ፔዜሽኪያን የኢራን ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የለውጥ አቀንቃኙ ዶክተር ማሱድ ፔዜሽኪያን ተፎካካሪያቸውን ወግ አጥባቂውን ሳኢድ ጃሊሊን በማሸነፍ የኢራን ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ። በምርጫው በተሰጠው ድምጽ ዶክተር ፔዜሽኪያን 53 ነጥብ 3 በመቶ ሲያገኙ፤ ተፎካካሪያቸው ጃሊሊ 44 ነጥብ 3 በመቶ…

25 ሰዎች ከሱዳን ግጭት ሸሽተው በባህር ሲጓዙ ሰጥመው ህይወታቸው ማለፉ ተሰማ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በማዕከላዊ ሱዳን ሲናር ግዛት ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ግጭት ሲሸሹ የተሳፈሩበት የእንጨት ጀልባ ተገልብጣ ቢያንስ 25 ሰዎች በባህር ሰጥመው ህይወታቸው እንዳለፈ ተነግሯል። የአስቸኳይ ድጋፍ ሰጪ ኃይል ወደ አካባቢው ሲገባ፣ ከአቡ ሁጃር ከተማ…

በብሪታኒያ ጠቅላላ ምርጫ የሌበር ፓርቲ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በብሪታኒያ በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የሌበር ፓርቲ ማሸነፉ ተገለፀ፡፡ ሌበር ፓርቲ እስካሁን ከብሪታኒያ 650 ወንበሮች 411 ያህሉን በማግኘት ነው ጠቅላላ ምርጫውን ማሸነፍ የቻለው፡፡ በውጤቱ መሰረት የሌበር ፓርቲው መሪ ኬር ስታርመር…

ሩሲያና ኢራን የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቃል ገቡ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ እና ኢራን በተለያዩ የጋራ ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቃል ገብተዋል። የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በካዛኪስታን በተካሄደው የሻንጋይ የትብብር ድርጅት (ኤስሲኦ) ከኢራን እና ኳታር መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት…

በህንድ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓት ላይ በተፈጠረ መተፋፈግ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 121 ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜናዊ ህንድ በሂንዱ ሀይማኖታዊ ፌስቲቫል ላይ በተፈጠረ መተፋፈግ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 121 መድረሱ ተገለፀ፡፡ አደጋው በህንድ ኡታር ፓራዴሽ ግዛት ሀታራስ በተባለው ስፍራ ላይ የሂንዱ እምነት ተከታዮች ሀይማታዊ ስነ ስርዓት እያከናወኑ በነበረበት…

ሩሲያ 5 የዩክሬን SU-27 ተዋጊ ጄቶችን ማውደሟን አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ በዩክሬን ላይ በሰነዘረችው ጥቃት አምስት SU-27 ተዋጊ ጄቶችን ማውደሟን የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ተዋጊ ጄቶቹ ላይ ጥቃት የተፈጸመው በኢስካንደር-ኤም ሚሳኤሎች እንደሆነ ያስታወቀችው ሩሲያ፤ በዩክሬን ማዕከላዊ ፖልታቫ ክልል…

ሩሲያ በዶንባስ ክልል የሚገኝ ተጨማሪ ግዛት መቆጣጠሯን ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ በዶንባስ ክልል የሚገኝ ተጨማሪ ግዛት መቆጣጠሯን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ኖቮፖክሮቭስኮይ በመባል የሚጠራው የዶኔስክ መንደር ከዩክሬን ሃይሎች ሙሉ በሙሉ ነጻ መደረጉን አረጋግጧል፡፡…

እስራኤል በሊባኖስ ላይ ወታደራዊ ጥቃት የምትፈጽም ከሆነ አስከፊ ጦርነት ይጠብቃታል – ኢራን

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) እስራኤል በሊባኖስ ላይ ወታደራዊ ጥቃት የምትፈጽም ከሆነ ከባድ አጸፋዊ እርምጃ ይጠብቃታል ስትል ኢራን አስጠነቀቀች፡፡ ኢራን ይህንን ያለችው እስራኤል በሊባኖስ የሂዝቦላህ ታጣቂ ቡድን ይዞታዎችላይ መጠነ ሰፊ ወታደራዊ ዘመቻ ለማካሄድ ዝግጁ ነኝ…

በኢራን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢራን በቅርቡ በሄሊኮፕተር መከስከስ አደጋ ህይወታቸውን ባጡት ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ቦታ አዲስ ፕሬዚዳንት ለመተካት አስቸኳይ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ መካሄድ ጀምሯል። በዚህም በዛሬው ዕለት የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ከማለዳ ጀምሮ ተከፍተው ኢራናውያን…