Fana: At a Speed of Life!

ለአትሌት ኮንስታብል ደሬሳ ገለታ የማዕረግ እድገት ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ በወንዶች ማራቶን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከተው እና 5ኛ ደረጃ በመያዝ በዲፕሎማ ላጠናቀቀው አትሌት ደሬሳ ገለታ የማዕረግ እድገት ሰጠ። በዚሁ መሠረት ለአትሌቱ የረዳት ኢንስፔክተር ማዕረግ መሰጠቱን…

አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎች ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተያዘው የበጀት ዓመት አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎች ላይ በትኩረት ይሠራል ሲሉ የባሕል እና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ አመላከቱ፡፡ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሕዝብ ተወካዮች፣ የክልል እና የከተማ አሥተዳደር የሥራ ኃላፊዎች በደሴ ከተማ…

ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና መስሪያ ቤትን ጎብኝተዋል፡፡ ሚኒስትሩ በብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ሲጎበኙ፥ ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ማድረጋቸው ተገልጿል፡፡ የፋይዳ…

በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ከ72 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያለው ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ግብርና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማቱ በቅርቡ በጎፋ ዞን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 72 ሚሊየን 87 ሺህ ብር ዋጋ ያለው ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ድጋፉም አንድ ተሽከርካሪን ጨምሮ ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶችን…

ሰዎችን አግተው ገንዘብ ሲቀበሉ ነበር የተባሉ የአሸባሪው ሸኔ አባላት ክስ ተመሰረተባቸው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ሰዎችን እያገቱ ገንዘብ በመቀበል የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ ነበር የተባሉ ሦስት የአሸባሪው ሸኔ ቡድን አባላት ክስ ተመሰረተባቸው። ክሱ የተመሰረተው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት ነው።…

በኢትዮጵያ በዝንጀሮ ፈንጣጣ የተያዘ ሰው የለም – ጤና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ እስከ አሁን ድረስ በዝንጀሮ ፈንጣጣ የተያዘ ሰው አለመኖሩን ጤና ሚኒስቴር አረጋገጠ፡፡ ዛሬ የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ተቋም (አፍሪካ ሲ ዲ ሲ) ባወጣው መግለጫ÷ በ13 የአፍሪካ ሀገራት 2 ሺህ 863 ሰዎች በዝንጀሮ ፈንጣጣ…

ለድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ለመስጠት የቀውስ ጊዜ ኮሙኒኬሽን ማኑዋል እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ለድንገተኛ አደጋዎች የተቀናጀ ምላሽ መስጠት የሚያስችል የቀውስ ጊዜ ኮሙኒኬሽን ማኑዋል እየተዘጋጀ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ፥ ከዚህ ቀደም ድንገተኛ…

የአዲስ ቱሞሮ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ ቱሞሮ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ግንባታን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የማስጀመሪያ መርሐ- ግብር ተካሂዷል፡፡ በ35 ሄክታር መሬት ላይ ከቻይናው "ሲሲሲሲ" ጋር በመተባበር የሚገነባው ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በከተማ ውስጥ አዲስ…

የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር የዘንድሮ ማዳበሪያ ማጓጓዝ ስራ ማጠናቀቁ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር የ2016 ዓ.ም የአፈር ማዳበሪያ ማጓጓዝ ስራውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡ 266 ሺህ 770 ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ በ103 ባቡሮች በማጓጓዝ ከዚህ ቀደም ከተመዘገበው ሁሉ የተሻለ አፈጻጸም…

የሀገራዊ ምክክር ሥራ ሒደት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያካተተና ተስፋ ሰጪ ነው – የሐረሪ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያከናወነ የሚገኘው ስራ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያካተተና ተስፋ ሰጪ መሆኑን በሐረሪ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደቱ ተሳታፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተናገሩ። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የሐረሪ…