Fana: At a Speed of Life!

ኢዜአ ያስገነባው ዘመናዊ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ያስገነባው ዘመናዊ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ተመርቋል፡፡ በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ÷ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት…

በኢትዮጵያና በጀርመን መካከል እየተተገበሩ ባሉ የልማት ስራዎች ላይ ውይይት ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ እና በጀርመን መካከል ስላለው በትምህርትና ሥልጠና፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በድህነት ቅነሳ እየተተገበሩ ያሉ ስራዎች ላይ ያተኮረ ውይይት መደረጉን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል አስታውቀዋል፡፡   በተጨማሪ…

በሐሰተኛ ሰነድ በማጭበርበር ከ13 ሚሊየን ብር በላይ ተቀብሎ ተሰውሯል የተባለው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር ዋለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐሰተኛ ሰነድ አጭበርብሮ ከባለሃብት 13 ሚሊየን 888 ሺህ ብር ተቀብሎ ተሰውሯል የተባለው ተጠርጣሪ ቱጁባ ቶልቻ ሰንበታ በቁጥጥር ሥር ዋለ፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እንዳስታወቀው÷ ተጠርጣሪው በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02…

በመዲናዋ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታ ለማከናወን ከሲጂሲኦሲ የግንባታ ተቋራጭ ጋር ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከዓለም ባንክ በተገኘ የ145 ሚሊየን ዶላር በአዲስ አበባ ከተማ የምስራቅ ተፋሰስ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታ ለማከናወን ከሲጂሲኦሲ የግንባታ ተቋራጭ ጋር ስምምነት ተፈረመ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር…

169 ሺህ 288 ዩኒት ደም ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ ከበጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች 202 ሺህ 509 ዩኒት ደም ለመሰብሰብ ታቅዶ 169 ሺህ 288 ዩኒት መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ደም እና ኅብረ-ኅዋስ ባንክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ በደም አሰባሰብ ሂደቱ÷ የመቱ፣ ሻሸመኔ፣…

የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮ 57 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ ሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ስድስት ወራት 57 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ አስታውቋል፡፡ የቢሮው ሃላፊ መስከረም ደበበ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷በበጀት ዓመቱ ከመደበኛ ግብር ከፋዮችና መዘጋጃ ቤት አገልግሎት 144…

ኬፕ ቨርዴ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ኬፕ ቨርዴ ሞሪታኒያን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡ ምሽት 2 ሰዓት በተደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ኬፕ ቨርዴ ሪያን ሜንዴዝ ባለቀ ደቂቃ ባስቆጠራት የፍጹም ቅጣት ምት 1 ለ 0 አሸንፋለቸ፡፡ ውጤቱን…

አቶ አደም ፋራህ የምስራቅ አፍሪካ አርብቶ አደሮች ኤክስፖን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የምስራቅ አፍሪካ አርብቶ አደሮች ኤክስፖን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝት መርሐ ግብሩ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አይሻ መሃመድ…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአይ ኤም ኤፍ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂኦርጂዬቫ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ይይቱ ከጣልያን-አፍሪካ ጉባዔ ጎን ለጎን መካሄዱን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ከተመድ የህፃናት ፈንድ የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ከተመድ የህፃናት ፈንድ የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ዳይሬክተር ኤትሌቫ ከዲሊን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም÷ድርጅቱ አስፈላጊ ሰብዓዊ ድጋፍን ለህፃናትና ሴቶች የበለጠ ተደራሽ ለማድረግ ሊሠራቸው በሚችላቸው ጉዳዮች ላይ…