Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጣለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው 10ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻል ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ አቻ ተለያይቷል፡፡ 9፡00 ላይ ሐዋሳ ከተማን የገጠመው መቻል 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡ የመቻልን ጎሎችም ምንይሉ ወንድሙ…

ኢትዮጵያና ሶማሊላንድ የደረሱበት ሥምምነት የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በር ይከፍታል – ቲቦር ናዥ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያና ሶማሊላንድ የደረሱበት ሥምምነት ዘመን ተሻጋሪ ግንኙነት በመመሥረት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በር የሚከፍት መሆኑን በኢትዮጵያ የቀድሞ የአሜሪካ አምባሳደር ቲቦር ናዥ ተናገሩ። አምባሳደር ቲቦር ናዥ ከሶማሊላንድ ክሮኒክል ጋር ባደረጉት ቃለ…

የባሕር በር ስምምነቱ የሚደገፍ ሀገራዊ አጀንዳ ነው – የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከሶማሊ ላንድ ጋር ያደረገችው የባሕር በር ስምምነት በቅንነት የሚወሰድ ሀገራዊ አጀንዳ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ድጋፍ እንደሚያደርጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት አስታወቁ፡፡ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በወቅታዊ…

በውኃ አካላት ላይ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ወደብን ጨምሮ በውኃ አካላት ላይ የማሪን ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአየር ትንበያ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፈጠነ ተሾመ…

የሜታ ቢዝነሥ ባለቤት ማርክ ዙከርበርግ በከብት እርባታ ሥራ ተሠማሩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሜታ ቢዝነሥ ኩባንያ ባለቤት እና ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ማርክ ዙከርበርግ ካላቸው ሥራ በተጨማሪ በከብት ዕርባታ የሥራ መስክ መሠማራታቸውን አስታወቁ፡፡ የከብት ዕርባታ ሥራውን የጀመሩት ከባለቤታቸው ጋር በመሆን በአሜሪካ ሃዋይ ግዛት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡…

የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ የዲጂታል ኢኮኖሚውን ለማሳደግ ፋይዳው የጎላ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የግል ዳታ ጥበቃ ረቂቅ አዋጅ ለብዙ ዓመታት ማገልገል እንዲችል ታሳቢ ተደርጎ በቀጣይ የሚጸድቅ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ በዛሬው ዕለት በግል ዳታ ጥበቃ ረቂቅ አዋጅ…

የወንጀል ድርጊቶችን ካሉበት ሆነው ለፖሊስ የሚያደርሱበት መተግበሪያ ሥራ ሊጀምር ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የወንጀል ድርጊቶችን ዜጎች ካሉበት ሆነው ለፖሊስ የሚያደርሱበት የሞባይል መተግበሪያ በቅርቡ በአዲስ አበባ ሥራ እንደሚጀምር የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል አስታወቁ፡፡ ፌዴራል ፖሊስ ከለውጡ በኋላ የሀገርንና የዜጎችን…

የሶማሌ ክልል የተማሪዎች ምዘና ፈተና መስጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል የ2016 የትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች አጋዥ የትምርት ድጋፍ ለመስጠት የተዘጋጀ የተማሪዎች ምዘና ፈተና ዛሬ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ መሰጠት ጀምሯል። የምዘና ፈተናው የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን…

አምባሳደር ምስጋኑ ከተመድ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሀና ቴቴ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም÷ በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እንቅስቃሴ፣ በወቅታዊ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ…

“ዲፕሎማሲያችን ለብሔራዊ ጥቅማችን” ዓውደ-ርዕይ ነገ በይፋ ይከፈታል

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) "ዲፕሎማሲ ለብሔራዊ ጥቅማችን" በሚል የሚካሄደው የዲፕሎማሲ ሣምንት ዓውደ-ርዕይ በነገው ዕለት በይፋ እንደሚከፈት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም (ዶ/ር) ዓውደ ርዕዩን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፤…