Fana: At a Speed of Life!

የ”ኩል ፖርት አዲስ” ፕሮጀክት ግንባታ ዘንድሮ ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለአትክልትና ፍራፍሬ ማቆያና መጓጓዣ የሚውለው የ"ኩል ፖርት አዲስ'' ፕሮጀክት ግንባታ ዘንድሮ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ባህርና ሎጂስቲክስ አስታወቀ። በኢትዮጵያ ባህርና ሎጂስቲክስ የወደብና ተርሚናል ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ምህረተአብ ተክሉ…

በማንዴላ ዋንጫ የአፍሪካ ቦክስ ውድድር ኢትዮጵያ 6 ሜዳሊያ በመሰብሰብ አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በማንዴላ አፍሪካ ቦክስ ውድድር ኢትዮጵያ ሶስት ብርና ሶስት የነሐስ በአጠቃላይ ስድስት ሜዳልያ በማግኘት ውድድሩን አጠናቃለች። በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵያ በሱራፌል አላዩ፣ ሚሊዮን ጨፎ እና ቤተል ወልዱ የነሃስ…

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ341 ሚሊየን በላይ ችግኝ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ከ341ሚሊየን በላይ ችግኝ ለመትከል እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡ የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ቢሮ ሃላፊ አስራት ገብረማሪያም (ዶ/ር)…

በአቡዳቢና ዱባይ ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ የሚነሱ ቅሬታዎች እየተፈቱ እንደሆነ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአቡዳቢና ዱባይ አካባቢ እየተሰጠ ባለው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎቶች ከዚህ ቀደም የሚነሱ ቅሬታዎች እየተፈቱ መሆኑን የኮሚኒቲ አባላት፣ ተወካዮችና አመራሮች ተናግረዋል። በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት…

የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ ከ19 ሺህ በላይ የምርት ጥራት ፍተሻ አገልግሎት ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ባለፉት 9 ወራት የአፈር ማዳበሪያን ጨምሮ ከ19 ሺህ በላይ የምርት ጥራት ፍተሻ አገልግሎት መስጠቱን አስታወቀ። የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር መዓዛ አበራ እንዳሉት÷ ድርጅቱ በዋናነት የጥራት ፍተሻ ላቦራቶሪ፣…

ፖፕ ፍራንሲስ በዩክሬን¬-ሩሲያና በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ያለው ጦርነት እንዲቆም በድጋሚ ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ በዩክሬ-ሩሲያ እንዲሁም በመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት እየተካሄደ ያለውን ጦርነት በማውገዝ የእርቀ ሰላም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ጳጳሱ በቫቲካን ከተማ በሚገኘው በሴንት ፒተር አደባባይ ለተሰበሰቡ ታዳሚዎች አሁንም ቢሆን በሀገራቱ…

በክልሉ ምቹ ስነ-ምህዳር ለመፍጠር ህብረተሰቡ የድርሻውን እንዲወጣ ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የአካባቢ ብክለትን በዘላቂነት በማስወገድ ለሰዎች የተስማማ ስነ-ምህዳር ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ህብረተሰብ የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ አሳሰቡ። "ብክለት ይብቃ ውበት ይንቃ" በሚል መሪ ሀሳብ…

የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ 28 ሚሊየን ዶላር ዋጋ ያላቸው ምርቶችን ለውጭ ገበያ አቀረበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ዘጠኝ ወራት የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከ28 ሚሊየን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው ምርቶችን ለውጭ ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ፡፡ በሌላ በኩል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ850 ለሚልቁ ወገኖች አዲስ የሥራ ዕድል መፈጠሩን የፓርኩ ሥራ አስኪያጅ…

በኦሮሚያ ክልል ጥብቅ የትራፊክ ቁጥጥር የሚደረግባቸው 1 ሺህ 12 ቦታዎች ተለዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ጥብቅ የትራፊክ ቁጥጥር የሚደረግባቸው 1 ሺህ 12 ቦታዎች መለየታቸው የክልሉ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ገለጸ። የኤጀንሲው የትራፊክ ደህንነት ማረጋገጫ ዳይሬክተር አቶ አለሙ ለማ በክልሉ እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመቆጣጠር…

ለ50 ሺህ መምህራንና የትምህርት አመራር የብቃት ስልጠና ሊሰጥ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በመጪው ክረምት ለ50 ሺህ መምህራንና የትምህርት አመራሮች የብቃት ስልጠና እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል ። ስልጠናው የትምህርት ጥራት ችግርን ለመቅረፍና የመምህራን ብቃትን ለማሳደግ ያለመ ሲሆን÷ በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ይሰጣል…