Fana: At a Speed of Life!

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጋ መስኖ 81 ሺህ ሄክታር በዘር ተሸፈነ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በበጋ መስኖ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 81 ሺህ ሄክታር በዘር መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ኃላፊ ኃይለማርያም ተስፋዬ እንዳሉት÷ በመስኖ የመጀመሪያው ዙር 121 ሺህ ሄክታር ለማልማት እየተሠራ ነው፡፡…

ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ለማቅረብ መዘጋጀታቸውን የሌማት ትሩፋት ተጠቃሚዎች ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ እንቁላል፣ ዶሮና የወተት ተዋፅዖ በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ለማቅረብ መዘጋጀታቸውን በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የሌማት ትሩፋት ተጠቃሚዎች ገለጹ፡፡ የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር የቤተሰባቸውን የምግብ ዋስትና…

በአዲስ አበባ ደርቢ ቡናማዎቹ ተጋጣሚያቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ደርቢ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በማሸነፍ ወሳኝ ሦስት ነጥብ አሳክቷል፡፡ 9፡00 ላይ በተደረገው ተስተካካይ ጨዋታ የቡናማዎቹን ብቸኛ ጎል ጫላ ተሺታ ከመረብ አሳርፏል፡፡ በጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ለመጋራት…

የሰላምን ጥሪ ለተቀበሉ ኃይሎች በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ስልጠና መሰጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን ሸዋ አካባቢ መንግሥት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ ኃይሎች በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡ የሰሜን ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ተክለየስ በለጠ የሰላም ጥሪውን በመቀበል ስልጠናውን ለመውሰድ ለተዘጋጁ አካላት…

ሀገራዊ ምክከሩ በስኬት እንዲጠናቀቅ እየሠራን ነው- ተፎካካሪ ፓርቲዎች

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የያዘው ግብ አንዲሳካ አባሎቻቸው ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች አስታወቁ፡፡ ሀገራዊ ምክክሩ የያዘው ግብ ሰፊ በመሆኑ ሂደቱ እንዲሳካ አባሎቻቸው ንቁ ተሳትፎ…

በጋዛ ጦርነቱ አሁንም ተባብሶ መቀጠሉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) እስራዔል የሃማስ ጠንካራ ይዞታ ነው ባለችው በደቡባዊ ጋዛ በሚገኘው ካን ዮኒስ ከተማ በታንክ እና በዓየር የታገዘ ጥቃት እያደረሰች መሆኗ ተሰምቷል፡፡ በከተማዋ የእስራዔል ወታደሮች እና የሃማስ ታጣቂዎች ከባድ የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን…

በቀጣይ 6 ወራት በ77 ከተሞች አዳዲስ የገበያ ማዕከላትን ለማቋቋም ይሠራል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት በቀጣይ ሥድስት ወራት በ77 ከተማ አስተዳደሮች እንደ አቅማቸው አዳዲስ የገበያ ማዕከላትን ለማቋቋምና ለማደራጀት እንደሚሠራ የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡ ቢሮው ከሰሜን ሸዋ ዞን እና ደብረ ብርሃን…

ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ በጎዴ ከተማ በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ በጎዴ ከተማ እየተካሄዱ የሚገኙ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል፡፡ የፕሮጀክቶቹን ግንባታ በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑ በጉብኝቱ ወቅት…

የዜጎችን ኢኮኖሚ ያገናዘበ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ይሠራል- የጋምቤላ ክልል

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሁሉንም ዜጎች ኢኮኖሚ ያገናዘበ የጤና አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እንደሚሠራ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ ገለጹ፡፡ የክልሉ የ2016 በጀት ዓመት ክልል አቀፍ የጤና መድኅን የንቅናቄ መድረክ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል። አቶ…