Fana: At a Speed of Life!

ዓዲ ሃገራይና ሽራሮ ከተሞች ዳግም የኤሌክትሪክ ሃይል አገኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜኑ የኢትዮጵያ  ክፍል ተፈሮ በነበረው ግጭት ምክንያት  የኤሌክትሪክ ሃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ ዓዲ ሃገራይና ሽራሮ ከተሞች ዳግም የኤሌክትሪክ ሃይል አግኝተዋል፡፡ ከሽሬ የኤሌክትሪክ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የሚያገኙት ዓዲ ሃገራይና ሽራሮ ከተሞች…

የ24 ሀገራት አምባሳደሮች በደብረብርሃን ለኢንቨስትመንት ዝግጁ የሆኑ አካባቢዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የ24 ሀገራት አምባሳደሮች በደብረ ብርሃን ከተማ ያለውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል፡፡   የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት…

በሂውስተን ግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች  አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ በተካሄደው የሂውስተን ግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጸታዎች ድል ቀንቷቸዋል፡፡ በሂውስተን የወንዶች ግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያዊው አትሌት ልዑል ገብረ ስላሴ አሸንፏል፡፡ አትሌት ልዑል ርቀቱን 1፡00፡34 በሆነ…

በአቶ ካሳሁን ጎፌ የተመራ ልዑክ ከጅቡቲ የንግድና ቱሪዝም ሚኒስትር ጋር ተወያየ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ካሳሁን ጎፌ የተመራ ልዑክ ከጅቡቲ የንግድና ቱሪዝም ሚኒስትር አሊ ዳውድ ጋር ተወያይቷል፡፡ በውይይታቸውም በሀገራቱ ዋና ዋና የወጪ ንግድ ምርቶች እና የንግድ ስምምነቶች ዙሪያ መክረዋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ…

አምባሳደሮች በጎንደር ከተማ የፋሲል ግንብን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ ሀገራት ኢትዮጵያን የሚወክሉ አምባሳደሮች በጎንደር ከተማ ታሪካዊና ጥንታዊውን የፋሲል ግንብ ጎብኝተዋል። በጉብኝት መርሐ ግብሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ተሳትፈዋል። አምባሳደሮቹ በቀጣይ ቱሪስቶች ወደ…

የምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ሪጅን የምርጫ ኮንግረስ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን መረጠ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በተደረገው የምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ሪጅን የምርጫ ኮንግረስ ለቀጣይ አራት ዓመታት ሪጅኑን የሚመሩ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን መርጠዋል፡፡ በዚህ መሠረትም ጄነራል ጃክሰን ቲዊ ከኬንያ ፕሬዚዳንት ሆነው ሲመረጡ÷ ሚስተር ዶሚኒክ ኡትሲት…

የጥምቀትን በዓል በአብሮነት፣እሴቱንና ባህላዊ ትውፊቱን ጠብቆ ማክበር ይገባል – ከንቲባ አዳነች

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብዝሃ ቋንቋና ሃይማኖት ባለቤት በሆነችው አዲስ አበባ የአደባባይ በዓል የሆነውን የጥምቀት በዓል በአብሮነት፣እሴቱንና ባህላዊ ትውፊቱን ጠብቆ ማክበር ይገባል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከር ሰላምን በመጠበቅና…

በመዲናዋ  የጥምቀት በዓል በሠላም እንዲጠናቀቅ  ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የከተራና የጥምቀት በዓል በሠላም እንዲጠናቀቅ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኅብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከከተማዋ…

የተለያዩ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ ጉዳይ ላይ እየመከሩ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ እና የሲዳማ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እየተወያዩ ነው፡፡ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ከፍተኛ አመራሮች  በወቅታዊ  ሀገራዊና ክልላዊ  ፖለቲካዊ ሁኔታዎች  እንዲሁም በሠላምና  ፀጥታ አዝማሚያዎች  ላይ…

በስፔን በተካሄደ የጎዳና ላይ ሩጫ አትሌት የዓለምዘርፍ የኋላው አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን ቫሌንሺያ በተካሄደ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ አትሌት የዓለምዘርፍ የኋላው አሸነፈች፡፡ ውድድሩን 29 ደቂቃ ከ19 ሰከንድ በመግባት ነው አትሌት የዓለምዘርፍ ያሸነፈችው፡፡