Fana: At a Speed of Life!

በበጎ ፈቃድ ተግባር ወጣቶች በሰላም ግንባታ የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተጀመረው የበጎ ፈቃድ ተግባር ወጣቶች ማህኅበራዊ እሴቶችን እንዲያዳብሩ በማድረግ በሰላም ግንባታ ተግባር የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተሰራ መሆኑን የሰላም ሚኒስቴር ገለፀ። ሚኒስቴሩ የብሔራዊ የበጎ ፈቃድ ማህበረሰብ አገልግሎት የ8ኛ ዙር በጎ…

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ ተማሪዎች ትክክለኛውን መረጃ ከትምህርት ሚኒስቴር ገጽ ላይ እንዲከታተሉም አሳውቋል፡፡ በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ነገ…

የሆራ አርሰዲ የኢሬቻ በዓል በሰላም መከበሩን የጋራ ግብረ-ኃይሉ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሆራ አርሰዲ የኢሬቻ በዓል የገዳ ሥርዓት እሴቶችን በጠበቀ መልኩ በሰላም ተከብሮ መጠናቁን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ፡፡ አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች፣ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎችና ከጎረቤት…

ከኢሬቻ አብሮነትን፣ ምስጋናን፣ ይቅርታና እርቅን ልንማር ይባል – የበዓሉ ታዳሚዎች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከኢሬቻ በዓል ምስጋናን፣ አብሮነትን፣ ይቅርታና እርቅን እንዲሁም ሰላምን ልንማር ይገባል ሲሉ የበዓሉ ታዳሚዎች ተናግረዋል፡፡ የሆራ አርሰዴ የኢሬቻ በዓል “ኢሬቻ የአንድነት እና የወንድማማችነት ዓርማ” በሚል መሪ ሃሳብ በቢሾፍቱ ከተማ በተለያዩ…

ኢሬቻን በዩኔስኮ በማስመዝገብ የቱሪስት መስሕብነቱን ማሳደግ ይገባል – የበዓሉ ታዳሚዎች

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 27 ፣2016፣ (ኤፍ ቢ ሲ) የኢሬቻ በዓል ራሱን ችሎ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) እንዲመዘገብ በማድረግ የቱሪስት መዳረሻነቱን ማሳደግ እንደሚገባ የበዓሉ ታዳሚዎች አመለከቱ፡፡ የሆረ አርሰዴ የኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ከተማ በተለያዩ…

ለለቅሶ የተጣለ ድንኳን ጥሶ የገባ አውቶቡስ ባደረሰው ጉዳት የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከጳውሎስ ሆስፒታል ወደ ሸጎሌ በሚወስደው መንገድ አለም ፀሐይ ድልድይ አካባቢ አንድ የከተማ አውቶብስ ለለቅሶ የተጣለ ድንኳን ጥሶ በመግባት ባደረሰው ጉዳት የሶስት ሰዎች ህይወት አለፈ። አደጋው የደረሰው ትናንት ቅዳሜ መስከረም 26…

የሆረ አርሰዴ የኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ተከበረ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሆረ አርሰዴ የኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ ከተማ ተከበረ ፡፡ በዓሉ “ኢሬቻ የአንድነት እና የወንድማማችነት ዓርማ” በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተከበረ የሚገኘው፡፡ በአከባበር ሥነ-ሥርዓቱ አባገዳዎች፣ ሀደ ሲንቈዎች፣ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፣…

ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከዓለም አቀፍ የክትባት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከዓለም አቀፍ የክትባት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጂሮም ኪም (ፕ/ር) ጋር ተወያተዋል፡፡ በውይይታቸውም÷ ዓለም አቀፉ የክትባት ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን እና…

በፕሪሚየርሊጉ ቶተንሃም ፣ ቼልሲ እና  ማንቼስተር ዩናይትድ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ8ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ቶተንሃም ፣ ቼልሲ  ማንቸስተር ዩናይትድ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፏል፡፡ በምሳ ሰዓት ከሜዳው ውጭ ሉተን ታውንን የገጠመው ቶተንሃም በሚኪ ቫንዴቬን ብቸኛ ጎል 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም…

አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካው ሴናተር ማይክ ሮንድስ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በአሜሪካ ሴናተር ማይክ ሮንድስ ከተመራ ልዑክ ጋር በጽሕፈት ቤታቸው ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሀገራዊ እና ቀጣናዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ…