Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደሮች የጎርጎራ ፕሮጀክትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ ሀገራት ኢትዮጵያን የሚወክሉ አምባሳደሮች የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው የጎርጎራ ፕሮጀክት ጎበኙ፡፡ አምባሳደሮቹ ፕሮጀክቱ ያለበትን ደረጃ ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን÷ የግንባታ ሂደቱን በተመለከተም ገለፃ ተደርጎላቸዋል።…

በተጠናቀቀው 6 ወር በአማራ ክልል 2 ሺህ 575 አልሚዎች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወሰዱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2015 ዓ.ም ግማሽ ዓመት በአማራ ክልል 2 ሺህ 575 አልሚዎች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱት አልሚዎች ከ144 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገባቸው…

በአዲስ አበባ ከተማና በዙሪያው ሽብር፣ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ…

በአዲስ አበባ ከተማና በዙሪያው ሽብር፣ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ገለፀ። የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ቀደም ሲል በአደረገው ግምገማ ስጋቶችን በመለየት በአዲስ አበባ ከተማና ዙሪያው…

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለሚ ኩራ በ90 ቀናት እየተሠሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለሚ ኩራ በ90 ቀናት እየተሠሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፡፡ ከንቲባዋ በለሚ ኩራ በ90 ቀናት እየተከናወኑ የሚገኙ የመንገድ አካፋይ የአረንጓዴ ልማት፣የአቅመ ደካሞች የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ፣…

ምክር ቤቱ ከዲፕሎማቶች ጋር የሀገርን የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማስፋፋት ያለመ ውይይት አካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት እና ነባርና አዳዲስ ዲፕሎማቶች የሃገሪቱን ንግድና ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት በጋራ መስራት ላይ ያለመ ውይይት አደረጉ። የመርሐ ግብሩ ዓላማ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ዲፕሎማሲ እና የንግድ አቅጣጫን…

በማንችስተር ደርቢ ዩናይትድ ሲቲን 2 ለ1 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ የማንችስተር ደርቢ ማንችስተር ዩናይትድ ማንችስተር ሲቲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ማስመዝገብ ችሏል። የማንችስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ማርከስ ራሽፎርድ እና ፈርናንዴዝ ሲያስቆጥሩ የማንችስተር…

ድምፃዊት ያለምወርቅ ጀምበሩ የ3ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድርን አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ድምፃዊት ያለምወርቅ ጀምበሩ የ3ኛው የፋና ላምሮት የ1 ሚሊየን ብር አሸናፊ ሆናለች፡፡ 3ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ የድምፃውያን ውድድር ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡ በዚህም ያለምወርቅ ጀምበሩ በአንደኝነት አሸናፊ ሆናለች። እንዲሁም…

ኢትዮጵያ ከሞዛምቢክ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ ያለምንም ግብ አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ7ኛው የአፍሪካ ሀገራት ቻምፒየን ሺፕ ቻን ውድድር የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ከሞዛምቢክ ጋር ያደረገችው ኢትዮጵያ ጨዋታዋን ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት አጠናቃለች። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አቻ መውጣቱን ተከትሎ አንድ ነጥብ በመያዝ በምድቡ ሁለተኛ…

ፊፋ የአርጀንቲና ብሄራዊ ቡድን በአለም ዋንጫ ስላሳየው ያልተገባ ባህሪ ምርመራ እንደሚያደርግ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ባለፈው ወር በኳታር በተካሄደው የአለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ፥ የ2018 ዓለም ዋንጫ አሸናፊዋን ፈረንሳይን በፍፁም ቅጣት ምት አሸንፋ ዋንጫውን ለሶስተኛ ጊዜ ባነሳችው በአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን "ያልተገባ ባህሪ"…

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የተለያዩ ምርቶችን ለውጭ ከሚያቀርቡ ላኪዎች ጋር ተወያየ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የተለያዩ ምርቶችን ለውጭ ገበያ ከሚያቀርቡ ላኪዎች ጋር በክልሉ ፕሬዚደንት ፅህፈት ቤት ተወያይቷል፡፡ በመድረኩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚደንት ሽመልስ አብዲሳ ፥ አንድ ሀገር የሚከበረው ጠንካራ ኢኮኖሚ…