Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከፕሬዚዳንት ኤልሲሲ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በግብጽ ካይሮ ከፕሬዚዳንት አብዱልፈታሕ ኤልሲሲ ጋር ተወያዩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው በኩል "በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ትብብር በሰፈነበት መንፈስ ውይይቶች አካሂደናል" ብለዋል።

በሶማሌ ክልል በአንድ ጀንበር 5 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል በአንድ ጀንበር 5 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት መጠናቀቁን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ አብዱልቃድር ረሺድ እንደገለጹት÷ 1 ሚሊየኑ በጅግጅጋ ከተማ ይተከላል፡፡ ቀሪው 4 ሚሊየን በክልሉ በተለያዩ ዞኖች…

አቶ ደመቀ የኢትዮ-ኬንያ ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር እየተሰራ መሆኑን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የኢትዮ-ኬንያ ሁለንተናዊ ግንኙነት የበለጠ እንዲጠናከር እየተሠራ መሆኑን ገለጹ። አቶ ደመቀ ነገ እና ከነገ በስቲያ በሚካሄደው 43ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አሥፈጻሚ ምክር…

ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) የኢጋድ ጥረት የቀጣናው ሀገራት በልማት እንዲዋሃዱ ነው አሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) ጥረት በቀጣናው መረጋጋት እንዲሰፍንና ሀገራቱ በልማት ሥራዎች እንዲዋሃዱ መሆኑን ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)ገለጹ፡፡ የኢጋድ ዋና ጸሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በለንደን “ቻትሃም”…

በሐረሪ ክልል ሕዝቡ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረሪ ክልል ሕዝቡ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በንቃት እንዲሳተፍ የክልሉ ግብርና ቢሮ ጥሪ አቀረበ፡፡ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ሻሚ አብዲ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በክልል ደረጃ 2 ነጥብ…

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ  አመራሮች በሰላምና ደኅንነት ላይ መከሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች በሰላምና ደኅንነት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያዩ፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ ÷ አዲስ አበባ…

አቶ ደመቀ መኮንን ኬንያ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኖሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ኬንያ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኖሩ፡፡ አቶ ደመቀ ነገ እና ከነገ በስቲያ በሚካሄደው 43ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አሥፈጻሚ ምክር ቤት ስብስባ…

ጎንደር አራዳ የኢትዮጵያ የክለቦች ሻምፒዮና ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐዋሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ዛሬ ተጠናቋል፡፡ በሻምፒና ውድድሩ ከተለያዩ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ 31 ክለቦች መሳተፋቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡ በማጠቃለያ…

የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር አስደናቂ እና ለበለጠ ሥራ የሚያነሳሳ ነው – የጀርመን ልዩ መልዕክተኛ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር አስደናቂ እና ለበለጠ ሥራ የሚያነሳሳ ፕሮጀክት መሆኑን በጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ የማሻሻያ ትግበራ ልዩ መልዕክተኛ ጄኒፈር ሊ ሞርጋን ገለጹ፡፡ ልዩ…

ለቀጣዮች 6 ወራት የቤት ኪራይ መጨመርም ሆነ ተከራይ ማስወጣት አይቻልም – የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከሐምሌ 2 ቀን 2015 እስከ ታኅሣሥ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር እና ተከራይን ማስወጣት እንደማይቻል አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡ ቀደም ሲል ከሰኔ 2 ቀን 2015 እስከ ሕዳር 2015፣ ከሕዳር 2 ቀን…