Fana: At a Speed of Life!

ከ100 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ የሚደረግባቸውን ክትባቶች በሀገር ውስጥ ለማምረት ያለመ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በየዓመቱ ከ100 ሚሊየን ዶላር በላይ ለግዢ ወጪ የሚደረግባቸውን ክትባቶች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለማምረት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ…

በለውጡ ሂደት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል – ብልፅግና ፓርቲ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት አምሥት የለውጥ ዓመታት ያጋጠሙ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመለወጥ ለዜጎች የምትመችና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ ሥኬታማ ሥራዎች መከናወናቸውን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ ምክትል…

የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ ፀደቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅን አስመልክቶ የቀረበለትን የውሳኔ ሐሳብ በአንድ ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፀደቀ፡፡ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓት ሁሉን አቀፍ፣ ወጥና አስተማማኝ የሀገሪቷ ነዋሪዎች የሚመዘገቡበት…

ከፀሐይ ክብደት 30 ቢሊየን እጥፍ የገዘፈ በርባኖስ ተገኘ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)በአፅናፈ-ሰማይ ላይ ከተዘረጉ በርካታ “ጋላክሲዎች” ይልቅ የገዘፈ በርባኖስ ወይም ጥልቁ ጥቁር ጉድጓድ “ብላክ ሆል” መገኘቱን የእንግሊዝ ተመራማሪዎች አስታወቁ። በዶክተር ጀምስ ናይቲንጌል የተመራው የእንግሊዙ ዱርሃም ዩኒቨርሲቲ የጥናት ቡድን…

በልምምድ ላይ የነበሩ ሁለት የአሜሪካ የጦር  ሄሊኮፕተሮች ተከሰከሱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ ኬንታኪ ግዛት በልምምድ ላይ የነበሩ ሁለት የአሜሪካ የጦር ሄሊኮፕተሮች መከስከሳቸውን የሀገሪቱ ጦር አስታውቋል፡፡ የአሜሪካ ጦር ቃል አቀባይ ኖንዲስ ቱርማን በሄሊኮፕተሩ ውስጥ የነበሩ የልምምድ ሰራተኞች  ቁጥር እና በሄሊኮፕተሩ መከስከስ…

ኢትዮጵያ ወደተሟላ ሰላም ለመሸጋገር የምታደርገውን ጥረት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ እየሰጠው ነው – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 21 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ወደተሟላ ሰላም ለመሸጋገር የምታደርገውን ጥረት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ እየሰጠው መሆኑን አስታወቀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለስ አለም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።…

በአዲስ አበባ የመደመር ትውልድ ለሕጻናትና ወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያና መጫወቻ ማዕከል ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የመደመር ትውልድ ለሕጻናትና ወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያና መጫወቻ ማዕከል ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ፡፡ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 የመደመር ትውልድ ለሕጻናትና ወጣቶች የስፖርት…

የኮሞሮስ ኘሬዚዳንት ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር የኮሞሮስ ኘሬዚዳንት አዛሊ አሱማኒ ምሽቱን አዲስ አበባ ገብተዋል። ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሰደር ምስጋኑ አርጋ አቀባበል አድርገውላቸዋል።…

የአውሮፓ ሕብረት ለኢትዮጵያ ከ60 ሚሊየን ዩሮ በላይ የሰብዓዊ ድጋፍ ሊያደርግ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ሕብረት 60 ነጥብ 5 ሚሊየን ዩሮ ለኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሊያደርግ መሆኑን በአዲስ አበባ የሕብረቱ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። ሕብረቱ በአጠቃላይ የ331 ሚሊየን ዩሮ ሰብዓዊ ድጋፍ ለአፍሪካ ቀንድ እንደሚሰጥ ይፋ ያደረገ ሲሆን÷ ይህም…

በኦሮሚያ ክልል በአምስት ዞኖች የኮሌራ ክትባት እየተሰጠ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2015(ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል የኮሌራ በሽታ በተከሰተባቸው አከባቢዎች ከ76 ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች ክትባት መስጠት መጀመሩን የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ፡፡ የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መንግሥቱ በቀለ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ በባሌ፣…