Fana: At a Speed of Life!

በምድብ 1 ኔዘርላንድስ እና ኢኳዶር ነጥብ ሲጋሩ ኳታር የመጀመሪያዋ ተሰናባች ሆናለች

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 16 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫው ምድብ 1 ኔዘርላንድስ እና ኢኳዶር ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል። ሁለቱ ቡድኖች ምሽት 1 ሰአት ላይ ባደረጉት ጨዋታ የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ፈጣን ጎል ተመዝግባለች። ጨዋታው አንድ አቻ ሲጠናቀቅ ኮዲ…

የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ በ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ያስገነባቸውን ኅንጻዎች አቶ ኡሞድ ኡጁሉ መረቁ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ በ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ገንብቶ ያጠናቀቃቸውን የግንባታ ፕሮጀክቶች አጠናቆ የክልሉ ርዕሠ-መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በተገኙበት ዛሬ አስመርቋል፡፡ ኀንፃዎቹ የተማሪዎች የመማሪያ ክፍሎችን፣ ማደሪያ ዶርሚተሪዎችን እና ሌሎች…

ኔይማር በጉዳት ምክንያት ከሁለት የምድብ ጭዋታዎች ውጭ መሆኑ ተረጋገጠ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብራዚላዊው የፊት መስመር ተጫዋች ኔይማር ጁኒየር በጉዳት ምክንያት በሁለት የምድብ ጭዋታዎች እንደማይሰለፍ ተገለፀ፡፡ ኔይማር ትናንት ምሽት ብራዚል ከሰርቢያ ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ባጋጠመው የቁርጭምጭሚት ጉዳት ምክንያት ነው ከሁለት የምድብ…

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 100 ነጥብ 75 ኪሎ ግራም ወርቅ ወደ ብሔራዊ ባንክ መግባቱ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአንድ ወር ከ15 ቀን ብቻ 100 ነጥብ 75 ኪሎ ግራም ወርቅ ወደ ብሔራዊ ባንክ መግባቱን የክልሉ ማዕድን ቁጥጥር ግብረ-ኃይል አስታውቋል፡፡ የማዕድን ቁጥጥር ግብረ-ኃይሉ ከጥቅምት 1 እስከ ኅዳር 15 ቀን 2015 ዓ.ም…

በዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሴኔጋል ኳታርን 3ለ1 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫ የምድብ 2 የሁለተኛ ዙር ጨዋታ  አፍሪካዊቷ ሴኔጋል  አዘጋጇን ሀገር ኳታር  3 ለ 1 አሸንፋለች፡፡ በኳታር አልቱማም ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቡሊያን ዲያ፣ ፋሙራ ዴዴሁ እና ባባ ዲየንግ  የሴነጋልን ጎሎች ሲያስቆጥሩ ሞሃመድ…

“ለሰላም ስምምነቱ ተፈፃሚነት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ሚና ሊወጣ ይገባል”- የአክሱም፣ ዓድዋና ሽረ ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “የትግራይ ህዝብ የሰላም አየር መተንፈስ ጀምሯል፤ ለሰላም ስምምነቱ ተፈፃሚነት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ሚና ሊወጣ ይገባል” ሲሉ የአክሱም፣ ዓድዋና ሽረ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡ በትግራይ ክልል የሚገኙ ነዋሪዎች በሰላም ስምምነቱ እጅግ መደሰታቸው ገልጸው÷…

የጋና የውጭ ጉዳይ ቢሮ የቴክኒክ ኮሚቴ ልዑካን በሳይንስ ሙዚየም ጉብኝት አደረጉ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 16 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጋና የውጭ ጉዳይ ቢሮ የመጡ የቴክኒክ ኮሚቴ ልዑካን በሳይንስ ሙዚየም ተገኝተው ለዕይታ ክፍት የሆኑ ምርትና አገልግሎቶችን ጎበኙ፡፡ ጎብኚዎቹ በሰጡት አስተያየት በኢመደአ በሚገኘው ኢትዮ-ሰርት ዲቪዥን በሀገሪቱ ላይ የሳይበር ጥቃት እንዳይከሰት…

ኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ግንባታ ተሞክሮዋን አካፈለች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ “በአፍሪካ ኅብረት የመሠረተ ልማት ግንባታ ፕሮግራም ሥር የምስራቅ አፍሪካ ክልላዊ ፕሮጀክቶች እና ቻይና በሚል በተዘጋጀ የውይይት መርሐ ግብር የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካፍለዋል። በመርሐ ግብሩ…

1 ሺህ 124 ዜጎች ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 16 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ 1 ሺህ 124 ዜጎች ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ዜጎቹ ዛሬ በተደረጉ በረራዎች መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል። ከትናንት በስቲያ 1 ሺህ 21…