Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ስለሺ ከ50 በላይ የአሜሪካ ባለሃብቶች ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ እና የኢፌዴሪ የገንዘበ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ ከ50 በላይ የአሜሪካ ባለሃብቶች ጋር ተወያዩ፡፡ ባለሃብቶቹ በዚህ ወቅት እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ ከአጎዋ መውጣቷ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ…

ብሔራዊ ባንክ ሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለሚጠቁሙ ወሮታ የሚከፈልበትን መመሪያ በሚመለከት ማብራሪያ ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9 ፣2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለሚጠቁሙ ወሮታ የሚከፈልበትን መመሪያ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ ባንኩ በቅርቡ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለሚጠቁሙ ዜጎች ወሮታ እከፍላለሁ ማለቱን ተከትሎ ነው ስለአጠቃላይ መመሪያው ዛሬ…

ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀም ከባድ የሙስና እና አስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈጽመዋል በተባሉ 3 የፖሊስ አባላት ላይ ክስ ተመሰረተ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዐቃቤ ሕግ በአዲስ አበባ ፖሊስ የአየር መንገድ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል ምርመራ ሃላፊን ጨምሮ ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀም ከባድ የሙስና እና አስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈጽመዋል ባላቸው 3 የፖሊስ አባላት እና ግብረአበሮቻቸው ላይ ክስ መሰረተ፡፡…

ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ በሸቤለይ ወረዳ ዘመናዊ የግመል ማራቢያ ማዕከልን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8 ፣2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ በሶማሌ ክልል ፋፈን ዞን ሸቤለይ ወረዳ ዘመናዊ የግመል ማራቢያ ማዕከልን ከልዑካቸው ጋር በመሆን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝቱ የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ…

የገንዘብ ግሽበትን እና የጥቁር ገበያን ለመቆጣጠር የተዘረጉ አዳዲስ አሰራሮች አበረታች ናቸው – የምጣኔ ሀብት ምሁራን

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት የገንዘብ ግሽበትን እና የጥቁር ገበያን ለመቆጣጠር በቅርቡ ይፋ ያደረጋቸው አዳዲስ አሰራሮች እና የቁጥጥር መንገዶች አበረታች ናቸው ሲሉ የምጣኔ ሃብት ምሁራን ገለጹ። ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የምጣኔ ሀብት ምሁራን…

ከሰሊጥና አኩሪ ዐተር ሰብሎች ከ11 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል – የግብርና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተያዘው የምርት ዘመን ከሰሊጥ እና አኩሪ ዐተር ሰብሎች ከ11 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፀው፥ ከ450 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥ ሰብል የተሸፈነ…

በኢትዮጵያ ላይ የተሞከሩ ከ1 ሺህ 600 በላይ የሳይበር ጥቃቶች ከሸፉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ በተለያዩ ተቋማት ላይ የተሞከሩ ከ1 ሺህ 600 በላይ የሳይበር ጥቃቶችን ማክሸፉን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስታወቀ። በመረጃና መረብ ደህንነት አስተዳደር የሳይበር ጥቃት ትንተና ቡድን መሪ አቤል…

አየር መንገዱ ሁለት ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ለማስገባት በዝግጅት ላይ መሆኑን ገለፀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደፊት ሁለት ተጨማሪ ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ለማስገባት በዝግጅት ላይ መሆኑን ገለፀ፡፡ ቦይንግ 787 ድሪም ላይነር አውሮፕላን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመጀመሪያ ጊዜ በረራ የጀመረበት 10ኛ አመት…

የቆዳ ተረፈ ምርትን ወደ ኮላ ጥሬ እቃነት የሚቀይር ፋብሪካ ወደ ስራ ገባ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቆዳ ተረፈ ምርትን ወደ ኮላ ጥሬ እቃነት የሚቀይር ፋብሪካ ወደ ስራ ገብቷል፡፡ "ጂያዚን ዛንግ ክረስት ኤንድ ፊኒሽድ ሌዘር ፕሮዳክትስ" የተባለ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ፋብሪካውን ወደ ስራ ማስገባቱ ተገልጿል፡፡ በዚህም የኢንዱስትሪ…

በመከላከያ ሠራዊት ስር በሚገኙ የትግራይ ከተሞች ሰብዓዊ ድጋፉን ለማሳለጥ እየተሠራ ነው- መንግሥት

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሰሞኑ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እጅ በገቡ የትግራይ ከተሞች ሰብዓዊ ድጋፉን ለማሳለጥ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ በትግራይ ክልል የሰብዓዊ አቅርቦት እና መሰረታዊ አገልግሎት ማስጀመርን…