Fana: At a Speed of Life!

በወላይታ ዞን ሁለት ጥርስ አብቅሎ የተወለደው ሕፃን

አዲስ አበባ፣ግንቦት 23፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በወላይታ ዞን በገሱባ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሁለት ጥርስ ያበቀለ ሕፃን መወለዱን ሆስፒታሉ አስታውቋል፡፡ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ፀጋዬ እንድሪያስ እንደገለጹት  ÷ ትናንት ሁለት ጥርስ ያለው ልጅ የተወለደ  ሲሆን  ይህ…

በአሶሳ ከተማ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መሰረተ ልማት ለመዘርጋት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሶሳ ከተማ በሁለት ዓመት የሚጠናቀቅ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መሰረተ ልማት መዘርጋት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ በከተማዋ ያለውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት እጥረት እና…

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሠላም ጥሪን ተቀብለው የሚመለሱ የጉሙዝ ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሠላም ጥሪን ተቀብለው የሚመለሱ የጉሙዝ ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ ተናገሩ፡፡ በክልሉ መተከል ዞን ዳንጉርና ማንዱራ…

በአማራ ክልል ከሰኔ 2 ጀምሮ ለ6 ነጥብ 2 ሚሊየን ሰዎች የኮቪድ-19 ክትባት ይሰጣል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ለ6 ነጥብ 2 ሚሊየን ሰዎች የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከያ ክትባት ከሰኔ 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ሊሰጥ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በጎንደር ከተማ ዛሬ በተሰጠው የሚዲያ ባለሙያዎች ስልጠና ፥ ሶስተኛ ዙር ክትባቱ…

ከ12 ሺህ በላይ ከድባጤ ወረዳ ተፈናቅለው የነበሩ ነዋሪዎች ወደቀያቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የተቀናጀ ኮማንድ ፖስት ባከናወናቸው የፀጥታ ስራዎች ተፈናቅለው ከነበሩት የድባጤ ወረዳ ነዋሪዎች መካከል ከ12ሺህ በላይ ወደቀያቸው መመለሳቸው ተገለጸ፡፡ ከህዳር ወር 2013 ዓ/ም ጀምሮ በተከሰተው የፀጥታ…

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከዋልያዎቹ ስብስብ አምስት ተጫዋቾችን ቀነሱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከዋልያዎቹ ስብስብ አምስት ተጨዋቾችን መቀነሳቸው ታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታውን ከማላዊ እና ግብፅ ጋር ለማድረግ አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ከጠሯቸው 28 ተጨዋቾች አምስት…

ቱርክ በፊንላንድ እና ስዊድን የኔቶ የአባልነት ጥያቄ ላይ የያዘችውን አቋም እንደማትቀይር አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2014 (ኤፍ በቢ ሲ) ቱርክ ለደህንነቷ እና ለኔቶ የወደፊት እጣ ፋንታ ስትል በፊንላንድ እና ስዊድን የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) የአባልነት ጥያቄ ላይ የያዘችውን አቋም እንደማትቀይር አስታወቀች። የቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ታይፕ…

የሲዳማና የኦሮሞ ህዝብን ለማጋጨት መታገል ለድካም ይዳርግ እንደሆን እንጂ አይሳካም -አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ

አዲስ አበባ፣ግንቦት 23፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የሲዳማና የኦሮሞን ህዝብ ለማጋጨት መታገል ለድካም ይዳርግ እንደሆን እንጂ አይሳካም ሲሉ የሲዳማ ክልል ሰላምና ደህንነት ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ተናገሩ፡፡ የኦሮሞና የሲዳማ ህዝብ የሰላም ኮንፈረንስ በሃዋሳ ከተማ ተካሂዷል፡፡…

አየር መንገዱ በሚቀጥለው ሰኔ 25 ወደ ቼናይ በረራ ሊጀምር ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2014 (ኤፍ በቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀጣዩ ሰኔ 25 ወደ ህንድ ቼናይ በሳምንት ሶሰት ጊዜ በረራ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡ ቼናይ በህንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አራተኛ መዳረሻ መሆኗን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ የኢትዮጵያ…

“ስለ ኢትዮጵያ” ሀገራዊ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) "ስለ ኢትዮጵያ" ሀገራዊ የምክክር መድረክ "ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች " በሚል መሪ ቃል በሐረር ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡ በመድረኩ የኢትዮጵያውያን የጋራ እሴቶች ለሀገር ህልውና ባላቸው ሚና ላይ ያተኮሩ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዋል።…