Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ ለቤት ኪራይ የወጣው ደንብ እስከሚሻሻል ድረስ የኪራይ ዋጋ መጨመር አይቻልም- ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለቤት ኪራይ የወጣው ደንብ እስከሚሻሻል ድረስ የኪራይ ዋጋ መጨመር የማይቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ። ከንቲባዋ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሰጡት መግለጫ ለቤት ኪራይ የወጣው ደንብ እስከሚሻሻል የቤት ኪራይ…

አስተዳደሩ የ14ኛ ዙር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓትን ለአርብ መዛወሩን አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ14ኛው ዙር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አወጣጥ ስነስርዓት ለአርብ መዛወሩን አስታወቀ። ከተማ አስተዳደሩ ዕጣ አወጣጥ ስነስርአቱን በነገው እለት ለማካሄድ ፕሮግራም ይዞ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ነገር ግን የህዝብ…

የዓለም የምግብ ፕሮግራም በአፋር ክልል ከ650 ሺህ በላይ ተረጂዎች ዕርዳታ ማከፋፈሉን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የምግብ ፕሮግራም በአፋር ክልል በግጭት እና በድርቅ ለተጎዱ ከ650 ሺህ በላይ ወገኖች የምግብ ዕርዳታ ማከፋፈሉን አስታውቋል፡፡ ዕርዳታውን ወደ ክልሉ ያደረሰው በየስድስት ሣምንታት ልዩነት በማጓጓዝ መሆኑን ጠቁሟል። ባለፈው ሳምንትም…

1ሺህ 24 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 24 ኢትዮጵያውያንን በዛሬው ዕለት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ ከተመላሾች ውስጥም አምስቱ ህጻናት መሆናቸውን ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ ለተመላሽ…

በኮንትሮባንድ የገቡ ሁለት ኮንቴነር ልባሽ ጨርቅ እና ጫማዎችን ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፖሊስ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ባደረጉት ክትትል በኮንትሮባንድ የገቡ ሁለት ኮንቴነር ልባሽ ጨርቅ እና ጫማዎችን መያዙን አስታወቀ፡፡   በህገ ወጥ መንገድ ወደ አዲስ አበባ ከተማ የገቡት ሁለት…

የአፍሪካ አየር መንገዶች በነዳጅ ዋጋ መናር 4 ቢሊየን ዶላር እንደሚያጡ ተነገረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በተያዘው ዓመት የአፍሪካ አየር መንገዶች በነዳጅ ዋጋ መናር ምክንያት ማግኘት የነበረባቸውን 4 ቢሊየን ዶላር ገቢ እንደሚያጡ የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር ገልጿል፡፡ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ተከትሎም የኬንያ አየር መንገድ የበረራ…

የስራ እና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ከዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የስራ እና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ከዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ሙሀመድ አብዲከር ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትሯ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው በነበራቸው ውይይት  በቀጠናው የክህሎት ልማት እና የወጣቶች የሥራ…

በአዲስ አበባ ከተማ በ40/60 እና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለ25 ሺህ 491 ቤቶች ነገ ዕጣ ይወጣባቸዋል

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በ3ኛው ዙር የ40/60 እና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ 25 ሺህ 491 ቤቶች ነገ ዕጣ እንደሚወጣባቸው ተገለጸ። በዕጣ አወጣጥ ሥነ ስርአት ዙሪያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ መግለጫ…

አብን በኦሮሚያ ክልል በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈፀሙ አሰቃቂ ጭፍጨፋዎችን የሚመረምር ልዩ አቃቤ ህግ በአዋጅ እንዲቋቋም እና የወንጀል ፈፃሚዎች በግልፅ ችሎት…

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል በንጹሃን ዜጎች ላይ  የተፈፀሙ አሰቃቂ  ጭፍጨፋዎችን የሚመረምር ልዩ አቃቤ ህግ በአዋጅ እንዲቋቋም እና የወንጀል ፈፃሚዎች በግልፅ ችሎት እንዲዳኙ ጠየቀ፡፡ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን)…

በሐረሪ ክልል በኢንቨስትመንት ስም መሬት ወስደው ባላለሙ አካላት ላይ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ አቅጣጫ ተቀመጠ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢንቨስትመንት ስም መሬት ወስደው ባላለሙ አካላት ላይ በአፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ የሐረሪ ክልል ካቢኔ አቅጣጫ አስቀመጠ፡፡ የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) በ2014 ዓ.ም የሴክተር መስሪያ ቤቶች ዕቅድ ክንውን እና…