Fana: At a Speed of Life!

በሰሜን ሸዋ ዞን ለሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖች ከ11 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢ ኤስ ዲ፣ ውመን ኢምፓወርመንት አክሽን እና ህይወት ኢትዮጵያ የተባሉ በጎ አድራጊ ድርጅቶች በጋራ በመሆን ለተፈናቃይ ወገኖች ከ11 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ድጋፉ የምግብ፣ የአልባሳትና በጦርነት ለተጎዱ ስድስት ትምህርት ቤቶች…

ለሕዝብ ደኅንነት ሲባል የተጀመረው ሕግ የማስከበር ሥራ ምንም ዓይነት ውስጣዊና ውጫዊ ተፅዕኖ የለበትም – ዶክተር ይልቃል ከፋለ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የተጀመረው የሕግ ማስከበር ሥራ ምንም ዓይነት ውጫዊና ውስጣዊ ጫና የሌለውና ዋነኛ ግቡም የሕዝብን ሠላምና ደኅንነት ማስከበር እንደሆነ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ገለጹ። ሠላም የሁሉም መሠረት ነው ያሉት…

በኢትዮጵያ ባንኮች ላይ ባነጣጠረ የማጭበርበር ወንጀል ከ1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ባላይ መመዝበሩ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚገኙ ባንኮችን ባነጣጠረ የማጭበርበር ወንጀል ከ1 ቢሊየን 896 ሚሊየን ብር በላይ መመዝበሩን በፍትህ ሚኒስቴር የተደረገ ጥናት አመላከተ። ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው በዚህ ጥናት ከ370 ቢሊየን ብር በላይ…

የዝንጀሮ ፈንጣጣ “በመካከለኛ” ደረጃ የዓለም የጤና ሥጋት መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዝንጀሮ ፈንጣጣ በመካከለኛ ደረጃ የዓለም የጤና ሥጋት መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ገለጸ፡፡ ቫይረሱ ሥጋት ሊሆን የሚችለው ለከባድ በሽታ ተጋላጭ ወደሆኑ ሕፃናት ከተዛመተ እና የበሽታ መከላከል አቅማቸው ወደተዳከመ የኅብረተሰብ ክፍሎች ከተሠራጨ…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የተገነባውን የኩላሊት እጥበት ማዕከል መረቁ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 22 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የተገነባውን የኩላሊት እጥበት ማዕከል መረቁ። በምረቃው መርሐ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ተገኝተዋል። አዲስ አበባን የጤና…

የአልጄሪያ – ኢትዮጵያ ፓርላማ ወዳጅነት ቡድን ተመሠረተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአልጄሪያ ብሔራዊ የሕዝብ ሸንጎ የኢትዮጵያና የአልጄሪያን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር የአልጄሪያ-ኢትዮጵያ ወዳጅነት ቡድን በዛሬው ዕለት ተመስርቷል። የአልጄሪያ-ኢትዮጵያ ወዳጅነት ቡድን ምሥረታን ምክንያት በማድረግ በፓርላማው የውጭ ግንኙነት…

ጠ/ሚ ዐቢይ በኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የምክትል መቶ አለቃነት ማዕረግ ላገኙ ምሩቃን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የምክትል መቶ አለቃነት ማዕረግ ላገኙ ምሩቃን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት…

በአማራ ክልል የመሬት ካዳስተር ቆጠራ ከ75 በመቶ በላይ መጠናቀቁ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ሲካሄድ የነበረው የመሬት ካዳስተር ቆጠራ ከ75 በመቶ በላይ መጠናቀቁን የክልሉ መሬት አሥተዳደር ገለጸ። በቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አወቀ ሲሳይ እንደገለጹት፥ አርሶአደሩ በመሬት ባለቤትነቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ዓለም…

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጌዴኦ ዞን ባህል ማዕከል ግንባታ ቦታ አስረከበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጌዴኦ ዞን ባህል ማዕከል ግንባታ የሚውል ቦታ በዛሬው ዕለት አስረክቧል፡፡ በስነ ስርዓቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎች፣ የደቡብ ክልል…

የኢትዮ-ጂቡቲ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች በአፋር ክልል የሚገጥማቸውን ችግር ለመፍታት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮ-ጂቡቲ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች በአፋር ክልል የሚገጥማቸውን ችግር ለመፍታት ክልሉ ከፌዴራል መንግስት ጋር በመተባበር እየሠራ መሆኑን ገለጸ። የክልሉ የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ የኢትዮ-ጂቡቲ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች በክልሉ…