Fana: At a Speed of Life!

የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት 623 መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)በሁለት ዙር በተሰጠው የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከተመዘገበው ውጤት 623 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ መመዝገቡን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በመጀመሪያው ዙር ፈተና የተመዘገበው ከፍተኛው ውጤት 563 ሲሆን÷ በሁለተኛው…

ፌደራል ፖሊስ ከሁለት ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በተለያዩ ዘርፎች ለመስራት ተስማማ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአውሮፓ ህብረት የጀርመን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ጂ.አይ.ዜድ) እና የጄኔቫ የፀጥታ ዘርፍ አስተዳደር ማዕከል (ዲካፍ) ጋር በፎረንሲክ ምርመራ ቴክኖሎጂዎችን ለማሟላት እና በስልጠና ዙሪያ አብሮ ለመስራት ተስማማ፡፡…

ኢትዮጵያና ኔዘርላድ በኢንዱስትሪ እና በግብርና ዘርፍ የሚያደርጉት ኢኮኖሚያዊ ትብብር በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ አድርጓል – የገንዘብ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያና የኔዘርላድ መንግስታት በኢንዱስትሪ እና በግብርና ዘርፍ የሚያደርጉት ኢኮኖሚያዊ ትብብር በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረጉን ገንዘብ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከግብርና ሚኒስቴር እና ከኔዘርላንድስ ኤምባሲ የተውጣጡ አመራሮች…

አሁን እየታየ ያለው የሙቀት መጠን በበልግ ወቅት የሚጠበቅ ነው – የሚቲዮሮሎጂ ኢኒስቲቲዩት

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የበልግ ወቅት በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሙቀት መጠን የሚመዘገብበት መሆኑንና አሁን እየተስተዋለ ያለው ነገር ከዚህ የተለየ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኢኒስቲቲዩት ገለፀ፡፡ የኢኒስቲቲዩቱ የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ…

በተባበሩት መንግስታት የፀረ-ሙስና ጉባኤ የኢትዮጵያ አፈፃፀም ግምገማ ሪፖርት ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁለተኛው ዙር የተባበሩት መንግስታት የፀረ-ሙስና ጉባኤ የኢትዮጵያ አፈፃፀም ግምገማ ረቂቅ ሪፖርት ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ውይይት እየተካሄደበት ነው፡፡ በጉባኤው ምዕራፍ ሁለት ሙስናን መከላከልና…

የሩሲያ ጦር የኬርሰን ክልልን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያ ጦር በዩክሬን እያካሄደ ባለው ወታደራዊ ዘመቻ በአገሪቱ ደቡባዊ ክፍል የምትገኘውን የኬርሰንን ክልል ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ሜጀር ጄኔራል ኢጎር ኮናሼንኮቭ እንዳሉት፥…

በአፋር ክልል ለተፈናቀሉ እና በሀርሱማ እና አፍዴራ ለተጠለሉ 7 ሺህ 500 ዜጎች ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ዓቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ቡድን ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በጋራ በመሆን በአፋር ክልል ለተፈናቀሉ እና በሀርሱማ እና አፍዴራ ለተጠለሉ 7 ሺህ 500 ዜጎች ድጋፍ አደረገ፡፡ የድጋፉ ተጠቃሚዎች ከአባላ፣ በርሃሌ፣ ማጋሌ እና ኢሪብቲ…

የብልጽግና ፓርቲ ህዝባዊ አደራውን ለመወጣት የሚያስችሉ እርምጃዎች መወሰዱን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ባካሄደው የመጀመሪያ ጉባኤው የፓርቲውን ውስጣዊ አንድነት የሚያጠናክሩ ውሳኔዎች መወሰኑንና የተጣለበትን ሕዝባዊ አደራ በአግባቡ ይወጣ ዘንድ በአመራሮች ላይ የማጥራት እርምጃ መወሰዱን አስታወቀ። በዚህም መሰረት…

በተሽከርካሪ እና እሳት አደጋ የ1 ሰው ህይወት ሲያልፍ 230 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ትናንት ምሽት በተከሰተ የተሽከርካሪ እና የእሳት አደጋ የ1 ሰው ህይወት ሲያልፍ 230 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገለፀ፡፡ የመኪና አደጋው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ትናንት ከምሽቱ 3 ሰዓት ከ14 ደቂቃ…

የሩሲያው ፕሬዚዳንት እና የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር የሩሲያ እና ዩክሬን ቀውስን አስመልክተው ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ናፍታሊ ቤኔት ጋር የሩሲያን እና የዩክሬንን ቀውስ በሰላማዊ መንገድ መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በስልክ ተወያዩ። ፕሬዜዳንት ፑቲን በሩሲያ እና በዩክሬን ተወካዮች…