Fana: At a Speed of Life!

በቪላ ዲ ማድሪድ የዓለም የቤት ውስጥ ቱር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የወርቅ ደረጃ በተሰጠው እና ትላንት ምሽት በስፔን በተካሄደው ቪላ ዲ ማድሪድ የዓለም የቤት ውስጥ ቱር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ ድል ቀንቷቸዋል። በዚህም መሠረት በወንዶች 3 ሺህ ሜትር ሰለሞን ባረጋ…

“ለኢትዮጵያ እንቁም” የተሰኘ ዘመቻ በለንደን ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለንደን በተከበረው 126ኛው የዓድዋ ድል በዓል የመታሰቢያ መርሃ-ግብር ላይ “ለኢትዮጵያ እንቁም” የተሰኘ ዘመቻ ተካሄደ፡፡ የኢትዮጵያ የዓለም ፌዴሬሽን የተሰኘ የጥቁሮች ህዝቦች የሆነ ድርጅት ዘመቻውን መምራቱን በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ…

ዶክተር ጌዲዮን ከተመድ ሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከተመድ ሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሼል ባችሌት ጋር ተወያዩ። ሚኒስትሩ በ49ኛው የተመድ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ እየተሳተፉ ይገኛል። ከስብሰባው ጎን ለጎን…

የትምህርት ጥራት ችግርን ለመቅረፍ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ባለድርሻ አካላት መረባረብ አለባቸው ተባለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ከዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል አባላትና መምህራን ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይቱ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ÷ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚስተዋለውን የትምህርት ጥራት…

ኤምባሲው በዩክሬን ለሚገኙና ከዩክሬን ወደ ፖላንድና ሌሎች አጎራባች አገሮች በመሄድ ላይ ላሉ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ማግኘት የሚችሉበት…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀርመን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በዩክሬን ለሚገኙና ከዩክሬን ወደ ፖላንድና ሌሎች አጎራባች አገሮች በመሄድ ላይ ላሉ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ማግኘት የሚችሉበት ሊንክ ይፋ አድርጓል፡፡ ኤምባሲው በሩስያ እና ዩክሬን መካከል…

በጋሞ ዞን 400 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ ለሚገነባው ትምህርት ቤት የመሠረት ድንጋይ ተጣለ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋሞ ዞን አስተዳደር 400 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ ለሚገነባው የሁለተኛ ደረጃ ሞዴል ትምህርት ቤት የመሠረት ድንጋይ ተጣለ። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ ትምህርት ቤቱ ትውልድን በመቅረጽ ሀገርን መረከብና መመራመር የሚችሉ እና…

የሞጆ ከተማ አስተዳደር በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 2 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር የሚገመት ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሞጆ ከተማ አስተዳደር በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን በተከሰተው ድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 2 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የምግብ እህል ድጋፍ አደረገ። ድጋፉን የሞጆ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ፀጋዬ ተክለሃና ለምሥራቅ ሐረርጌ ዞን አስተዳዳሪ…

የክተት አዋጅ በታወጀባት ወረኢሉ ከተማ 126ኛው የዓድዋ ድል በዓል ተከበረ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዳግማዊ አፄ ሚኒልክ የክተት አዋጅ ባወጁባት ወረኢሉ ከተማ 126ኛው የዓድዋ ድል በዓል በድምቀት ተከብሯል። በድል በዓሉ ላይ የተገኙት በመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዋና ሀላፊ ሜጀር ጀኔራል አህመድ ሀምዛ፥ የኢትዮጵያውያን…

የጣሊያን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የኢትዮጵያ የቡና ማሠልጠኛ ማዕከልን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጣሊያን ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሪያና ሴሬቲ የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የኢትዮጵያ የቡና ማሠልጠኛ ማዕከል ጎበኘ፡፡ በጉብኝት መርሃ-ግብሩ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች እንዲሁም…

በጦርነቱ ምክንያት ከዩክሬን ወደ ጎረቤት ሀገራት ለመሻገር የሚሞክሩ አፍሪካውያን የዘረኝነት ተጽእኖ እየደረሰብን ነው አሉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያ - ዩክሬን ጦርነትን በመሸሽ ከዩክሬን ወደ ተለያዩ ጎረቤት ሀገራት ለመሻገር የሚሞክሩ አፍሪካውያን በቆዳ ቀለማቸው ምክንያት ተጽእኖ እየደረሰባቸው መሆኑን ተናገሩ። ጦርነቱን በመሸሽ ከዩክሬን ወደ ተለያዩ ጎረቤት ሀገራት ለመሸሽ በሞከሩ…