Fana: At a Speed of Life!

በ24 ሰዓታት ውስጥ 46 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው፤ የ1 ሰው ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 3 ሺህ 410 የላብራቶሪ ምርመራ 46 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 701 መድረሱን የጤና…

የአፍሪካ ቀንን በማስመልከት “የህንድ-አፍሪካ አጋርነት” በሚል መሪ ቃል የቪድዮ ኮንፈረንስ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአፍሪካ ቀንን በማስመልከት “የህንድ-አፍሪካ አጋርነት እና በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት  ቀጣይ እርምጃዎች” በሚል ርዕስ የቪድዮ ኮንፈረንስ ተካሄደ። በህንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ትዝታ ሙሉጌታ በቪዲዮ ኮንፈረንሱ ላይ የተሳተፉ ሲሆን፥ ቀኑን…

በአንድነት የምንፈልጋትን ኢትዮጵያ ለመገንባት በዓላማ፣ በሐሳብና በትጋት እንነሣ-ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ግንቦት 18፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአንድነት የምንፈልጋትን ኢትዮጵያ ለመገንባት በዓላማ፣ በሐሳብና በትጋት እንነሣ ሲሉ ጥሪ አቀረቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ እንዳስታወቁት÷ ኢትዮጵያውያን ብልጽግና ይመጥናቸዋል፣ ይገባቸዋልም…

ደቡብ ኮሪያ ለኢትዮጵያ 16 ሺህ ቶን ሩዝ በእርዳታ ለገሰች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ደቡብ ኮሪያ በድንበር ተሻጋሪ የምግብ ድጋፍ ፕሮግራሟ አማካኝነት ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአራት የመካከለኛው ምስራቅና የአፍሪካ አገራት 50 ሺህ ቶን የሩዝ ምርት ድጋፍ ማድረጓን የአገሪቱ የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። አገሪቱ በዓለም የምግብ ድርጅት…

በኦሮሚያ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የተላለፉ ከ1 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የተላለፉ ከ1 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ። በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እንዳስታወቁት፥ በኦሮሚያ ክልል የኮሮና ቫይረስ…

በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ እየጨመረ በመሄዱ የሚወሰዱ እርምጃዎችና ስራዎች እየጠበቁ እንደሚሄዱ መንግስት ገለፀ 

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ እየጨመረ እየሄደ በመሆኑ የሚወሰዱ እርምጃዎች እና ስራዎች እየጠበቁ እንደሚሄዱ መንግስት ገለፀ። የኮቪድ19 ወረርሽኝ መከላከልና መቆጣጠር የሚኒስቴሮች ኮሚቴ አስተባባሪ ሴክሬታሪያት የኢፌዴሪ የሰላም ሚኒስትር…

ኳታር ለኢትዮጵያ የኮሮና መከላከያ የሚውሉ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኳታር መንግስት በኳታር የልማት ፈንድ አማካኝነት ለኮሮናቫይረስ መከላከያ የሚውሉ የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገች።   ድጋፍ የተደረጉ የህምክና መሳሪያዎቹ 9 ቶን የሚመዝኑ ሲሆን፥ ኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል…

ናይጄሪያ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ከውጭ ምግብ የምታስመጣበት ገንዘብ የላትም-ፕሬዚዳንት ሙሀመዱ ቡሀሪ 

አዲስ አበባ፣ግንቦት 18፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ)የናይጄሪያው ፕሬዝዳንት  ሙሀመዱ ቡሀሪ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ባስከተለው ችግር አገሪቱ  ከውጭ ምግብ የምታመጣበት ምንም ገንዘብ እንደሌላት ገለጹ ፡፡ ስለሆነም አርሶ አደሮች አገሪቱን ለመመገብ የሚያስችል በቂ ምርት ማምረት አለባቸው ብለዋል…

የዓለም ጤና ድርጅት ኮሮናቫይረስን ለማከም ይረዳል በተባለው ሃይድሮክሲክሎሮኪን የወባ መድሃኒት ላይ የሚያደርገውን ሙከራ አቋረጠ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለም ጤና ድርጅት ኮሮናቫይረስን ለማከም እንደሚረዳ የተነገረው ሃይድሮክሲክሎሮኪን በተባለው የወባ መድሃኒት ላይ ሲያደርግ የነበረውን ሙከራ አቋረጠ። ሙከራው የተቋረጠው መድሃኒቱ ከደህንነት ጋር ተያይዞ አደጋ ሊያደርስ ይችላል በሚል ስጋት…