ስፓርት
ምርጥ ብቃት ላይ የሚገኙ የፊት መስመር ተጫዋቾች …
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለቡድናቸው እና ለሀገራቸው ግቦችን በማስቆጠር ጥሩ ጊዜ እያሳለፉ የሚገኙ ምርጥ የፊት መስመር ተጫዋቾች ናቸው፡፡
ኖርዌያዊው ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ፣ እንግሊዛዊው ሃሪ ኬን እና ፈረንሳዊው ኪሊያን ምባፔ፡፡
የ25 ዓመቱ የማንቼስተር ሲቲ የፊት መስመር ተጫዋች ሃላንድ በ2025/26 የውድድር ዓመት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ባደረጋቸው 11 ጨዋታዎች 14 ኳሶችን ከመረብ ጋር በማገናኘት የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃን ይዟል፡፡
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ደግሞ ለሲቲ…
Read More...
ከ20 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ስፖርት ውስጥ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ስፖርት በበርካታ ኃላፊነቶች ላይ አገልግለዋል፤ አሁንም እያገለገሉ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት፣ የአፍሪካ ፓርላማ አፈ ጉባኤ፣ የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነት እና ሌሎችም የሰሩባቸውና እየሰሩባቸው ያሉ ኃላፊነቶች ናቸው።
በሙያ የጥርስ…
ከ17 ዓመት በታች የሴካፋ ዋንጫ በፋና+
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ማጣርያ የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ኢትዮጵያ ከሩዋንዳ የሚያደርጉት ጨዋታ በፋና+ ቻናል በቀጥታ ይተላለፋል።
ጨዋታው ነገ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል።
በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የሴካፋ ዋንጫ 10 የምስራቅ እና መካከለኛ አፍሪካ ሀገራት…
ኪሊያን ምባፔ ወደ ማድሪድ ተመለሰ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ26 ዓመቱ ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት ወደ ሪያል ማድሪድ ተመልሷል፡፡
ትናንት ምሽት ፈረንሳይ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ዩክሬንን 4 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ ሁለት ግቦችን ቢያስቆጥርም ጉዳት አጋጥሞታል፡፡
በዚህም ተጫዋቹ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ስብስብን በመልቀቅ ወደ ክለቡ ሪያል ማድሪድ ለመመለስ…
ሚኬል አርቴታ አማትሪያን…
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል መሪ ሚኬል አርቴታ አማትሪያን የተወለደው በፈረንጆቹ 1982 በስፔን ሳን ሴባስቲያን ሲሆን፤ የእግር ኳስ ህይወቱ ጅማሬና ዕድገት በካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ነው፡፡
በባርሴሎና የታሰበውን ያክል የጨዋታ ጊዜ ባለማግኘቱ ወደ ፈረንሳዩ ክለብ ፓሪስ ሴን ዠርመ በማቅናት 18 ወራትን በውሰት አሳልፏል፡፡…
ሰር ዴቪድ ጆሴፍ ቤካም…
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ባህል እና እግር ኳስ ልዩ መለያ - ሰር ዴቪድ ጆሴፍ ቤካም፡፡
ትውልዱ በፈረንጆቹ 1975 በእንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን የሆነው ዴቪድ ቤካም የእንግሊዝ እግር ኳስ እና ባህል ልዩ መለያ ነው፡፡
የቀድሞ አማካይ በአራት የተለያዩ ሀገራት ሊጎች በመጫወት ዋንጫዎችን ያሸነፈ ብቸኛው እንግሊዛዊ ተጫዋች…
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ባህል ስፖርት ም/ፕሬዚዳንት ቦታን ማግኘቷ የሚበረታታ ነው – ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 1 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ባህል ስፖርት አባል ሀገር ከመሆን አልፋ የምክትል ፕሬዚዳንትነት ቦታን ማግኘቷ የሚበረታታ ነው አሉ የኢትዮጵያ ባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ።
የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ…