Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ የዓለማችን ውዱ ክለብ መሆኑን ፎርብስ ይፋ አድርጓል፡፡ ፎርብስ መጽሔት በዛሬው ዕለት ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት÷ ሪያል ማድሪድ በ9 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ዋጋ የዓለማችን ውዱ ክለብ መሆን ችሏል፡፡ ሪያል ማድሪድ በውድድር ዓመቱ ስኬታማ ጊዜ ባያሳልፍም ለተከታታይ አምስተኛ ዓመት የዓለማችን ውዱ ክለብ በመሆን በቀዳሚነት ተቀምጧል፡፡ ሌላኛው የስፔን ክለብ ባርሴሎና በ7 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር 2ኛ ሲሆን÷ ማንቼስተር ዩናይትድ ደግሞ በ7 ነጥብ 2 ቢሊየን…
Read More...

ሚኬል አርቴታ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ሽልማትን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2025/26 ውድድር ዓመት ምርጥ አሰልጣኝ ሽልማትን አሸንፏል፡፡ ሚኬል አርቴታ በውድድር ዓመቱ የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ከአርሰናል ጋር ያነሳ ሲሆን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግም ክለቡን ለፍፃሜ አድርሷል። አርሴን ቬንገር በፈረንጆቹ 2003/4 የፕሪሚየር ሊጉ…

ኤሲሚላን ከአሰልጣኝ ማሲሚሊያኖ አሌግሪ ጋር ተለያየ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጣሊያኑ ክለብ ኤሲሚላን ከአሰልጣኝ ማሲሚሊያኖ አሌግሪ ጋር ተለያይቷል፡፡ ሚላን በሴሪ ኤው የውድድር ዓመቱ የመጨረሻ ጨዋታ በካግሊያሪ 2 ለ 1 መሸነፉን ተከትሎ 5ኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ ተገዷል፡፡ በዚህም በተከታታይ ሁለት ዓመታት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ቦታን ማግኘት ሳይችል ቀርቷል፡፡…

ሻምፒዮኑ አርሰናል ዋንጫውን ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው አርሰናል በዛሬው ዕለት ዋንጫውን ተረክቧል፡፡ ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል÷ በዚህ ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡ በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመራው የሰሜን ለንደኑ…

በኬፕ ታውን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳንላም ኬፕ ታውን የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸንፈዋል፡፡ በወንዶች አትሌት መሀመድ ኢሳ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ55 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል፡፡ በርቀቱ የተሳተፈው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ይሁንልኝ አዳነ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ በመግባት ሁለተኛ…

በሺያመን ዳይመንድ ሊግ አትሌት አዲሱ ይሁኔ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የዳይመንድ ሊግ ሁለተኛ መዳረሻ በሆነችው የቻይናዋ ሺያመን ከተማ በወንዶች 5 ሺህ ሜትር አዲሱ ይሁኔ አሸንፏል። አትሌት አዲሱ 12፡57.32 በሆነ ሰዓት ውድድሩን ያጠናቀቀ ሲሆን ይህም የዓመቱ የዓለማችን ፈጣኑ ሰዓት እንዲሁም የውድድሩ አዲስ ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል። ሌላኛው ኢትዮጵያዊው አትሌት ቢኒያም…

ኒኮ ኦራይሊ የፕሪሚየር ሊጉ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማትን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የማንቼስተር ሲቲ ተጫዋች ኒኮ ኦራይሊ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማትን አሸንፏል፡፡ ከክለቡ አካዳሚ የተገኘው የ21 ዓመቱ ተጫዋች ከደጋፊዎች በተሰበሰበ ድምፅ ነው የምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማትን ማሸነፍ የቻለው፡፡ ኒኮ ከአርሰናል ጋር እልህ አስጨራሽ የዋንጫ ፉክክር ባደረገው…