Fana: At a Speed of Life!

75 ሺህ ወገኖችን ለመድረስ ያለመ ነጻ የጤና ምርመራ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረሪ ክልል 75 ሺህ ወገኖችን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነጻ የጤና ምርመራና ሕክምና አገልግሎት መስጠት ተጀመረ። አገልግሎቱ በተለይ ከፍለው መታከም የማይችሉ ወገኖችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ያሲን አብዱላሂ ተናግረዋል፡፡…

በአፋር ክልል የክረምት ነጻ የጤና ምርመራ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፋር ክልል 40 ሺህ ወገኖችን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ የክረምት ነጻ የበጎ ፈቃድ የጤና ምርመራ ተጀምሯል፡፡ የክረምት ነጻ የበጎ ፈቃድ የጤና ምርመራና ሕክምናው ከ40 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች አገልግሎቱን ለመስጠት ያለመ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር መረጃ…

የወባ በሽታን ለመቆጣጠር ጠንካራ የክትትልና ቁጥጥር ስራ እየተሰራ ነው – ጤና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የወባ በሽታን ለመቆጣጠር ጠንካራ የክትትል እና ቁጥጥር ስራ እየተሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ የወባ፣ የኮሌራና የኩፍኝ ስርጭትን በሚመለከት መግለጫ ሲሰጡ እንዳሉት፥ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት…

አልኮሆል ያለአግባብ መጠቀምና ሱሰኝነት ያለው ተፅዕኖ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አልኮሆል ያለአግባብ መጠቀም እና ጥገኛ መሆን በህይወትዎ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል። አልኮሆልን ያለአግባብ መጠቀም ማለት አልኮልን ከመጠን ያለፈ ወይም በብዛት መጠቀም ሲሆን፤ የአልኮሆል ጥገኛነት ለተወሰነ ጊዜ አልኮሆልን ያለማቋረጥ ሲጠቀሙ እና…

የኮሌራ በሽታ መንስዔ እና ምልክቶች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኮሌራ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በማስከትል በሰውነት ውስጥ የሚገኝን ፈሳሽ አሟጥጦ በማስወጣት፣ አቅምን በማዳክም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሞት ሊዳርግ የሚችል በሽታ ነው። ኮሌራ ቫይብሮ ኮሌራ በተባለ ተህዋስ አማካኝነት የሚመጣና አንጀትን የሚያጠቃ በሽታ…

ኮይካ ለኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክር ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ለኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡ ኮይካ በሥነ-ተዋልዶና ቤተሰብ እቅድ ዙሪያ መረጃ ተደራሽ በማድረግ ግንዛቤ ማስጨበጥ የሚያስችሉ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ…

በአማራ ክልል የወባ በሽታ ስርጭት እየተስፋፋ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የወባ በሽታ ስርጭት በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በክልሉ የሚስተዋለውን የወባ ሥርጭት መግታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ  በባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ የአማራ ክልል…

የኩፍኝ መንስዔዎችና ምልክቶች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኩፍኝ ማለት ሚዝልስ (Measles) በተባለ ረቂቅ ተህዋስ አማካኝነት የሚመጣ ተላላፊ የሆነ በሽታ ነው። በአብዛኛው ክትባት ያልወሰዱ ህፃናት ላይ የሚከሰት ቢሆንም አዋቂዎች ላይም ሊከሰት ይችላል። የኩፍኝ በሽታ በዋናነት በትንፋሽ የሚተላለፍ…

ከስርዓተ-ምግብና ጤና ጋር የተያያዙ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ሊሆኑ ነው ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤይድ) ጋር በመተባበር ከስርአተ-ምግብ እና ጤና ጋር የተያያዙ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ እንደሚሆኑ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የዩኤስኤይድ ኒውትሪሽን ቡድን አባላት ስርአተ-ምግብ፣ ልማትና ሰላምን አጣምሮ በኢትዮጵያ…

የስክሪን ብርሃን ለልጆች አይን ጤንነት ያለው አሉታዊ ተፅዕኖ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አሁን ላይ ልጆች ስክሪን ላይ (ስልክ፣ ቲሌቪዥን) የሚያሳልፉት ጊዜ በርከት እያለ መጥቷል፤ ይህ ደግሞ የልጆች የአይን ጤንነነት ላይ ጉዳት ያስከትላል። በዚህም ወላጆች ልጆች ስክሪን የሚያዩበትን የቆይታ ጊዜ መወሰን ወይም መገደብ አለባቸው፡፡…